ኢዮብ 26 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 26:1-14

ኢዮብ

1ኢዮብም እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“ኀይል የሌለውን ምንኛ ረዳኸው!

ደካማውንስ ምንኛ አዳንኸው!

3ጥበብ የሌለውን ምንኛ መከርኸው!

ታላቅ ዕውቀትንስ ምንኛ ገለጥህለት!

4ይህን ቃል እንድትናገር የረዳህ ማን ነው?

የማንስ መንፈስ በአንደበትህ ተጠቀመ?

5“ከውሆችና በውስጣቸው ከሚኖሩ በታች ያሉ፣

የሙታን መንፈስ በጭንቅ ላይ ናቸው።

6ሲኦል26፥6 የዕብራይስጡ ቅጅ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ አንዳንድ ቅጆች ግን፣ ሞት ይላሉ። በእግዚአብሔር ፊት ዕራቍቷን ናት፤

የጥፋትንም26፥6 ዕብራይስጡ፣ አባዶን ይላል። ስፍራ የሚጋርድ የለም።

7የሰሜንን ሰማይ በሕዋው ላይ ዘረጋው፤

ምድርንም እንዲያው በባዶው ላይ አንጠለጠላት።

8ውሆችን በደመናዎቹ ይጠቀልላል፤

ክብደታቸውም ደመናዎቹን አይሸነቍርም።

9ደመናዎቹን በላዩ ዘርግቶ፣

የሙሉውን ጨረቃ ፊት ይጋርዳል።

10ለብርሃንና ለጨለማ ድንበር ይሆን ዘንድ፣

በውሆች ላይ የአድማስ ክበብ አበጀ።

11የሰማይ ምሰሶዎች ይንቀጠቀጣሉ፤

በተግሣጹም ይደነግጣሉ።

12በኀይሉ ባሕርን ያናውጣል፤

በጥበቡም ረዓብን ይቈራርጣል።

13በእስትንፋሱ ሰማያትን አጠራ፤

እጁም ተወርዋሪውን እባብ ወጋች።

14እነዚህ የሥራው ዳር ዳር ናቸው፤

ስለ እርሱ የሰማነው ምንኛ አነስተኛ ነው!

የኀይሉንስ ነጐድጓድ ማን ሊያስተውል ይችላል?”

Thai New Contemporary Bible

โยบ 26:1-14

โยบ

1โยบจึงตอบว่า

2“ท่านช่วยคนหมดแรงได้มากเสียจริง!

ช่วยพยุงแขนที่อ่อนล้าได้เยี่ยมจริงนะ!

3คำแนะนำที่ท่านให้แก่คนไม่มีปัญญานั้นช่างยอดเยี่ยม!

ท่านได้แสดงความเข้าใจที่ลึกซึ้งเสียนี่กระไร!

4ใครหนอช่วยให้ท่านพูดออกมาอย่างนี้ได้?

วิญญาณดวงใดหนอที่พูดออกมาผ่านปากของท่าน?

5“บรรดาผู้ตายต้องทุกข์ทรมาน

ทั้งบรรดาคนที่อยู่ใต้น้ำและทุกชีวิตในนั้น

6แดนมรณาเปลือยเปล่าต่อหน้าพระเจ้า

แดนพินาศไร้สิ่งปกปิด

7พระเจ้าทรงคลี่ท้องฟ้าด้านเหนือบนความว่างเปล่า

และทรงแขวนโลกไว้เหนือที่เวิ้งว้าง

8พระองค์ทรงห่อหุ้มน้ำไว้ในเมฆของพระองค์

และเมฆก็ไม่ได้แตกกระจายเพราะน้ำหนักของมัน

9พระองค์ทรงคลี่เมฆ

ทรงบดบังจันทร์เพ็ญ

10พระองค์ทรงกำหนดเส้นขอบฟ้าที่ทะเล

เป็นพรมแดนระหว่างความสว่างกับความมืด

11เสาของฟ้าสวรรค์สั่นคลอน

เมื่อพระองค์ทรงกำราบ

12และโดยฤทธิ์อำนาจของพระองค์ ทะเลก็สงบราบคาบ

โดยพระปรีชาญาณ ทรงหั่นราหับออกเป็นชิ้นๆ

13ฟ้าสวรรค์งดงามโดยลมปราณของพระเจ้า

พระหัตถ์ของพระองค์ทรงแทงพญางูที่กำลังเลื้อยไป

14เหล่านี้เป็นเพียงสิ่งเล็กน้อยที่พระองค์ทรงกระทำ

เป็นแค่เสียงกระซิบแผ่วๆ ที่เราได้ยินเกี่ยวกับพระองค์เท่านั้น!

แล้วใครเล่าจะสามารถเข้าใจความเกรียงไกรแห่งฤทธิ์อำนาจของพระองค์ได้?”