ኢያሱ 14 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 14:1-15

ከዮርዳኖስ በስተ ምዕራብ ስላለው ምድር አከፋፈል

1ካህኑ አልዓዛር፣ የነዌ ልጅ ኢያሱና የእስራኤል የየነገዱ ጐሣ አባቶች የደለደሉላቸው፣ እስራኤላውያንም በከነዓን ምድር የወረሱት ርስት ይህ ነው። 2ርስታቸውም እግዚአብሔር በሙሴ አማካይነት በሰጠው ትእዛዝ መሠረት፣ ለዘጠኙ ነገድና ለእኩሌታው ነገድ በዕጣ ተከፋፈለ። 3ሙሴ ለሁለቱ ነገድና ለእኩሌታው፣ የዮርዳኖስን ምሥራቅ ክፍል ርስት አድርጎ ሰጣቸው፤ ሌዋውያኑ ግን አብረዋቸው እንዲካፈሉ አላደረገም፤ 4የዮሴፍ ልጆች ምናሴና ኤፍሬም ሁለት ነገዶች ሆነው ነበርና፤ ለሌዋውያኑ ግን ከሚኖሩባቸው ከተሞች እንዲሁም ለበግ፣ ለፍየልና ለከብት መንጎቻቸው መሰማሪያ እንዲሆን አብሮ የተከለለላቸውን ምድር ብቻ እንጂ ሌላ አልሰጣቸውም። 5ስለዚህ እስራኤላውያን እግዚአብሔር ሙሴን ባዘዘው መሠረት፣ ምድሪቱን ተካፈሉ።

ኬብሮን ለካሌብ ተሰጠች

6የይሁዳም ሰዎች በጌልገላ ወደ ኢያሱ ቀረቡ፤ ከዚያም የቄኔዛዊው የዮፎኒ ልጅ ካሌብ እንዲህ አለው፤ “እግዚአብሔር በቃዴስ በርኔ ስለ አንተና ስለ እኔ፣ የአምላክ ሰው ለሆነው ለሙሴ የተናገረውን ታውቃለህ። 7የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ ምድሪቱን እንድሰልል ከቃዴስ በርኔ በላከኝ ጊዜ የአርባ ዓመት ሰው ነበርሁ፤ እኔም ትክክለኛውን ማስረጃ ይዤለት መጣሁ፤ 8አብረውኝ ወደዚያ የወጡት ወንድሞቼ ግን፣ የሕዝቡ ልብ በፍርሀት እንዲቀልጥ አደረጉ፤ ሆኖም እኔ አምላኬን እግዚአብሔርን በፍጹም ልቤ ተከተልሁት። 9ስለዚህም ሙሴ በዚያች ዕለት፣ ‘አምላኬን እግዚአብሔርን በፍጹም ልብህ ተከትለኸዋልና እግርህ የረገጣት ምድር ለዘላለም የአንተና የዘርህ ርስት ትሆናለች’14፥9 ዘዳ 1፥36 ይመ ብሎ ማለልኝ።

10“አሁንም እነሆ፤ ልክ እግዚአብሔር እንዳለው ይህን ለሙሴ ከተናገረበት ጊዜ አንሥቶ እስራኤል በምድረ በዳ ሲንከራተት እኔን አርባ አምስት ዓመት በሕይወት ጠብቆ አኑሮኛል፤ ይኸው ዛሬ ሰማንያ አምስት ዓመት ሆነኝ። 11ሙሴ በላከኝ ጊዜ የነበረኝ ብርታት ዛሬም አብሮኝ አለ፤ ልክ እንደዚያን ጊዜ ሁሉ አሁንም ወደ ጦርነት ለመሄድ ኀይሉም ብርታቱም አለኝ። 12አሁንም እግዚአብሔር በዚያች ዕለት ቃል የገባልኝን ይህችን ኰረብታማ አገር ሰጠኝ። ዔናቃውያን በዚያ እንደ ነበሩና ከተሞቻቸውም ታላላቅና የተመሸጉ እንደ ሆኑ ያን ጊዜ አንተው ራስህ ሰምተሃል፤ ሆኖም ልክ እርሱ እንዳለው በእግዚአብሔር ርዳታ አሳድጄ አወጣቸዋለሁ።”

13ከዚያም ኢያሱ የዮፎኒን ልጅ ካሌብን ባረከው፤ ኬብሮንንም ርስት አድርጎ ሰጠው። 14ስለዚህም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ኬብሮን የቄኔዛዊው የዮፎኒ ልጅ የካሌብ ርስት ሆነች፤ የእስራኤልን አምላክ እግዚአብሔርን በፍጹም ልቡ ተከትሏልና። 15ኬብሮን ቀድሞ ከዔናቃውያን ሁሉ ታላቅ በሆነው በአርባቅ ስም ቂርያት አርባቅ ተብላ ትጠራ ነበር።

ከዚያም ምድሪቱ ከጦርነት ዐረፈች።

Persian Contemporary Bible

يوشع 14:1‏-15

تقسيم كنعان به حكم قرعه

1‏-2زمينهای تصرف شدهٔ كنعان، بين نه قبيله و نيم به حكم قرعه تقسيم شد، چون خداوند به موسی دستور داده بود كه زمينها به حكم قرعه تقسيم شوند. العازار كاهن، يوشع و رؤسای قبايل بنی‌اسرائيل اين قرعه‌كشی را انجام دادند. 3‏-4موسی قبلاً زمينهای سمت شرقی رود اردن را به دو قبيله و نيم داده بود. (قبيلهٔ يوسف شامل دو قبيله به نامهای منسی و افرايم بود. قبيلهٔ لاوی نيز گرچه به طور كلی از زمين محروم بود، ولی شهرهايی برای سكونت و چراگاههايی برای چرانيدن حيوانات به ايشان داده شد.) 5پس تقسيم زمين، مطابق دستوراتی كه خداوند به موسی داده بود، انجام گرفت.

زمين كاليب

6روزی عده‌ای از مردان قبيلهٔ يهودا به جلجال نزد يوشع آمدند. يكی از آنها كه كاليب، پسر يَفُنه قَنِزی بود، از يوشع پرسيد: «آيا به خاطر داری وقتی در قادش برنيع بوديم، خداوند دربارهٔ من و تو به موسی چه گفت؟ 7در آن زمان من چهل ساله بودم. موسی ما را از قادش برنيع به سرزمين كنعان فرستاد تا وضع آنجا را بررسی كنيم. من آنچه را كه حقيقت داشت به او گزارش دادم، 8اما برادران ديگر كه با من آمده بودند، قوم را از رفتن به كنعان ترسانيدند. ولی چون من خداوند، خدای خود را پيروی می‌كردم، 9موسی به من قول داد زمينی كه قدم در آن گذاشته‌ام تا ابد از آن من و فرزندانم باشد. 10حال چنانكه می‌بينی، از آن هنگام كه در بيابان سرگردان بوديم تاكنون كه چهل و پنج سال از آن می‌گذرد خداوند مرا زنده نگاه داشته است. با اينكه هشتاد و پنج سال از عمرم می‌گذرد 11هنوز مانند زمانی كه موسی ما را برای بررسی سرزمين كنعان فرستاد، سالم و قوی هستم و می‌توانم باز مثل گذشته سفر كنم و با دشمنان بجنگم! 12پس اكنون كوهستانی را كه خداوند وعده‌اش را به من داده است، به من بده. بدون شک به خاطر می‌آوری وقتی برای بررسی اوضاع به كنعان رفته بوديم، عناقی‌های غول‌آسا در آن كوهستان زندگی می‌كردند و شهرهای ايشان بزرگ و حصاردار بود؛ اما به ياری خداوند، من آنها را از آنجا بيرون خواهم راند، همانطور كه خداوند فرموده است.»

13‏-14يوشع كاليب را بركت داد و حبرون را به او بخشيد، زيرا كاليب از صميم دل خداوند، خدای اسرائيل را پيروی كرده بود. حبرون تا امروز نيز از آن كاليب می‌باشد. 15(پيش از آن حبرون، قريهٔ اربع ناميده می‌شد. اربع نام بزرگترين دلاور عناقی‌ها بود.)

در اين زمان، در سرزمين كنعان صلح برقرار بود.