ኢያሱ 12 – NASV & SNC

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 12:1-24

የተሸነፉ ነገሥታት ስም ዝርዝር

1እንግዲህ እስራኤላውያን ድል ያደረጓቸውና ከዮርዳኖስ ማዶ በስተ ምሥራቅ የሚገኘውን የዓረባን ክፍል በሙሉ ይዞ፣ ከአርኖን ሸለቆ እስከ አርሞንዔም ተራራ የሚዘልቀውን ግዛታቸውን የወሰዱባቸው ነገሥታት እነዚህ ናቸው፤

2መቀመጫውን በሐሴቦን አድርጎ የገዛው የአሞራውያን ንጉሥ ሴዎን፣

ከአርኖን ሸለቆ ዳርቻ ላይ ካለችው ከአሮዔር ማለት ከሸለቆው መካከል አንሥቶ፣ የአሞናውያን ወሰን እስከ ሆነው እስከ ያቦቅ ወንዝ ድረስ ገዝቷል፤ ይህም የገለዓድን እኩሌታ ይጨምራል።

3እንዲሁም ከኪኔሬት ባሕር12፥3 “ገሊላ” ናት። እስከ ሙት12፥3 የሙት ባሕር፣ የጨው ባሕርም ይባላል። ባሕር ያለውን ምሥራቃዊውን ዓረባ፣ እስከ ቤት የሺሞትና ከዚያም በስተ ደቡብ እስከ ፈስጋ ተራራ ግርጌ ድረስ ገዝቷል።

4መቀመጫውን በአስታሮትና በኤድራይ አድርጎ የገዛውና ከመጨረሻዎቹ ከራፋይም ዘሮች አንዱ የሆነው የባሳን ንጉሥ ዐግ፣

5የአርሞንዔምን ተራራ፣ ሰልካንን፣ ባሳንን ሁሉ እስከ ጌሹራውያንና እስከ ማዕካታውያን ድንበሮች እንዲሁም ከገለዓድ እኩሌታ እስከ ሐሴቦን ንጉሥ እስከ ሴዎን ወሰን ድረስ ገዝቷል።

6የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴና እስራኤላውያን እነዚህን ድል አደረጉ፤ የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴም ምድራቸውን ለሮቤል፣ ለጋድና ለምናሴ ነገድ እኩሌታ ርስት አድርጎ ሰጣቸው።

7እንግዲህ ኢያሱና እስራኤላውያን ከዮርዳኖስ በስተ ምዕራብ ድል ያደረጓቸው የምድሪቱ ነገሥታት እነዚህ ናቸው፤ ግዛታቸውም በሊባኖስ ሸለቆ ውስጥ ካለው ከበኣልጋድ ተነሥቶ በምዕራብ ሴይር እስካለው እስከ ሐላቅ ተራራ ይደርሳል፤ ኢያሱም የእነዚህን ነገሥታት ምድር እንደ ነገዳቸው አከፋፈል ለእስራኤላውያን በማከፋፈል ርስት አድርጎ ሰጣቸው። 8ይህም ተራራማው አገር፤ በስተ ምዕራብ ያለው የኰረብታ ግርጌ፣ ዓረባ፣ የተራራው ሸንተረሮች፣ ምድረ በዳውና ነጌብ ማለት የኬጢያውያን፣ የአሞራውያን፣ የከነዓናውያን፣ የፌርዛውያን፣ የኤዊያውያንና የኢያቡሳውያን ምድር ነው፤ ነገሥታቱም እነዚህ ናቸው፤

9የኢያሪኮ ንጉሥ፣ አንድ፤

ቤቴል አጠገብ ያለችው የጋይ ንጉሥ፣ አንድ፤

10የኢየሩሳሌም ንጉሥ፣ አንድ፤

የኬብሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

11የየርሙት ንጉሥ፣ አንድ፤

የለኪሶ ንጉሥ፣ አንድ፤

12የዔግሎን ንጉሥ፣ አንድ፤

የጌዝር ንጉሥ፣ አንድ፤

13የዳቤር ንጉሥ፣ አንድ፤

የጌድር ንጉሥ፣ አንድ፤

14የሔርማ ንጉሥ፣ አንድ፤

የዓራድ ንጉሥ፣ አንድ፤

15የልብና ንጉሥ፣ አንድ፤

የዓዶላም ንጉሥ፣ አንድ፤

16የመቄዳ ንጉሥ፤ አንድ፤

የቤቴል ንጉሥ፣ አንድ፤

17የታጱዋ ንጉሥ፣ አንድ፤

የኦፌር ንጉሥ፣ አንድ፤

18የአፌቅ ንጉሥ፣ አንድ፤

የለሸሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

19የማዶን ንጉሥ፣ አንድ፤

የሐጾር ንጉሥ፣ አንድ፤

20የሺምሮን ሚሮን ንጉሥ፣ አንድ፤

የአዚፍ ንጉሥ፣ አንድ፤

21የታዕናክ ንጉሥ፣ አንድ፤

የመጊዶ ንጉሥ፣ አንድ፤

22የቃዴስ ንጉሥ፣ አንድ፤

በቀርሜሎስ የሚገኘው የዮቅንዓም ንጉሥ፣ አንድ፤

23በዶር ኰረብታ12፥23 ወይም፣ “ናፎት ዳር” ማለት ነው። የሚገኘው የዶር ንጉሥ፣ አንድ፤

በጌልገላ የሚገኘው የጎይም ንጉሥ፣ አንድ፤

24የቲርሳ ንጉሥ፣ አንድ።

እነዚህ በድምሩ ሠላሳ አንድ ነገሥታት ናቸው።

Slovo na cestu

Jozue 12:1-24

1Tito pak jsou králové té země, kteréž pobili synové Izraelští, a opanovali zemi jejich, za Jordánem k východu slunce, od potoku Arnon až k hoře Hermon i všecky roviny k východu: 2Seon, král Amorejský, kterýž bydlil v Ezebon, a panoval od Aroer, kteréž leží při břehu potoka Arnon, a u prostřed potoka toho, a polovici Galád, až do potoka Jabok, kterýž jest na pomezí synů Ammon, 3A od rovin až k moři Ceneret k východu, a až k moři pouště, jenž jest moře slané k východu, kudyž se jde k Betsimot, a od polední strany ležící pod horou Fazga. 4Pomezí také Oga, krále Bázan, z ostatků Refaimských, kterýž bydlil v Astarot a v Edrei, 5A kterýž panoval na hoře Hermon a v Sálecha, i ve vší krajině Bázan až ku pomezí Gessuri a Machati, a nad polovicí Galád, ku pomezí Seona, krále Ezebon. 6Mojžíš, služebník Hospodinův, a synové Izraelští pobili je; a dal ji Mojžíš služebník Hospodinův k vládařství pokolení Rubenovu, Gádovu a polovici pokolení Manassesova. 7Tito pak jsou králové země té, kteréž pobil Jozue a synové Izraelští za Jordánem k západu, od Balgad, kteréž jest na poli Libánském, až k hoře lysé, kteráž se táhne až do Seir, a dal ji Jozue pokolením Izraelským k vládařství po dílích jejich, 8Na horách i na rovinách, i po polích, i v údolích, i na poušti a na poledne, zemi Hetejského, Amorejského, Kananejského, Ferezejského, Hevejského a Jebuzejského: 9Král Jericha jeden, král Hai, kteréž bylo na straně Bethel, jeden; 10Král Jeruzalémský jeden, král Hebron jeden; 11Král Jarmut jeden, král Lachis jeden; 12Král Eglon jeden, král Gázer jeden; 13Král Dabir jeden, král Gader jeden; 14Král Horma jeden, král Arad jeden; 15Král Lebna jeden, král Adulam jeden; 16Král Maceda jeden, král Bethel jeden; 17Král Tafua jeden, král Chefer jeden; 18Král Afek jeden, král Sáron jeden; 19Král Mádon jeden, král Azor jeden; 20Král Simron Meron jeden, král Achzaf jeden; 21Král Tanach jeden, král Mageddo jeden; 22Král Kedes jeden, král Jekonam z Karmelu jeden; 23Král Dor z krajiny Dor jeden, král z Goim v Galgal jeden; 24Král Tersa jeden. Všech králů třidceti a jeden.