ኢያሱ 1 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 1:1-18

እግዚአብሔር ኢያሱን አዘዘ

1የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ ከሞተ በኋላ፣ እግዚአብሔር የሙሴን አገልጋይ የነዌን ልጅ ኢያሱን እንዲህ አለው፤ 2“እነሆ፤ ባሪያዬ ሙሴ ሞቷል፤ እንግዲህ አሁንም አንተና ይህ ሕዝብ ሁሉ ተነሡ፤ ለእስራኤላውያን ወደምሰጣቸው ምድር ለመግባት የዮርዳኖስን ወንዝ ተሻገሩ። 3ለሙሴ በሰጠሁትም ተስፋ መሠረት፣ እግራችሁ የሚረግጠውን ቦታ ሁሉ እሰጣችኋለሁ። 4የርስታችሁ ዳርቻ ከምድረ በዳው እስከ ሊባኖስ፣ ከታላቁ ወንዝ ከኤፍራጥስ አንሥቶ፣ የኬጢያውያንን ምድር በሙሉ ይዞ፣ በምዕራብ በኩል እስከ ታላቁ ባሕር1፥4 የሜድትራኒያን ባሕር ይደርሳል። 5በሕይወት በምትኖርበት ዘመን ሁሉ ማንም አይቋቋምህም፤ ከሙሴ ጋር እንደ ነበርሁ ሁሉ ከአንተም ጋር እሆናለሁ፤ ከቶ አልጥልህም፤ አልተውህም።

6“ጽና፤ ለቀደሙት አባቶቻቸው እሰጣችኋለሁ ብዬ የማልሁላቸውን ምድር እንዲወርሱ፣ ይህን ሕዝብ የምትመራው አንተ ነህና በርታ። 7አይዞህ፤ ብቻ አንተ በርታ፤ ባሪያዬ ሙሴ የሰጠህን ትእዛዝ ሁሉ በጥንቃቄ ጠብቅ፤ በምትሄድበትም ሁሉ እንዲሳካልህ፣ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አትበል። 8ይህ የሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፤ በውስጡ የተጻፈውን ሁሉ በጥንቃቄ እንድትፈጽመውም ቀንም ሆነ ሌት ከሐሳብህ አትለየው፤ ይህን ካደረግህ ያሰብኸው ይቃናል፤ ይሳካልም፤ 9በምትሄድበት ሁሉ እግዚአብሔር አምላክህ ከአንተ ጋር ነውና አይዞህ፤ በርታ፤ ጽና፤ አትፍራ፤ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን?”

10ኢያሱም የሕዝቡን አለቆች እንዲህ ሲል አዘዛቸው፤ 11“ወደ ሰፈር ግቡ፤ ለሕዝቡም፣ ‘ስንቃችሁን አዘጋጁ፤ ከአሁን ጀምሮ ባሉት ሦስት ቀናት ውስጥ ዮርዳኖስን ተሻግራችሁ፣ እግዚአብሔር አምላካችሁ ርስት አድርጎ የሚሰጣችሁን ምድር ገብታችሁ ትወርሳላችሁ’ በሏቸው።”

12ኢያሱ የሮቤልን ነገድ፣ የጋድን ነገድና የምናሴን ነገድ እኩሌታ እንዲህ አላቸው፤ 13የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ እንዲህ ሲል የሰጣችሁን ትእዛዝ አስቡ፤ ‘እግዚአብሔር አምላካችሁ ያሳርፋችኋል፤ ይህችንም ምድር ይሰጣችኋል።’ 14ሚስቶቻችሁና ልጆቻችሁ እንዲሁም ከብቶቻችሁ ሙሴ በሰጣችሁ ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ ባለው ምድር ይቈዩ፤ ነገር ግን ተዋጊዎቻችሁ ሁሉ፣ ከነሙሉ ትጥቃቸው፣ ከወንድሞቻችሁ ቀድመው ይሻገሩ፤ እናንተም ከወንድሞቻችሁ ጐን ተሰለፉ። 15ይህም፣ እግዚአብሔር እስኪያሳርፋቸውና ለእናንተም እንዳደረገው ሁሉ፣ እነርሱም እግዚአብሔር አምላካችሁ የሰጣቸውን ምድር እስኪወርሱ ድረስ ነው። ከዚህ በኋላ እናንተም ተመልሳችሁ የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ የሰጣችሁን፣ በፀሓይ መውጫ ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ ያለውን ምድር ትወርሳላችሁ።”

16እነርሱም ለኢያሱ እንዲህ ሲሉ መለሱለት፤ “ያዘዝኸንን ሁሉ እናደርጋለን፤ ወደምትልከንም ሁሉ እንሄዳለን። 17ለሙሴ ሙሉ በሙሉ እንደ ታዘዝን ሁሉ፣ ለአንተም እንታዘዛለን፤ ብቻ እግዚአብሔር አምላክህ ከሙሴ ጋር እንደ ነበረ፣ አሁንም ከአንተ ጋር ይሁን። 18በትእዛዝህ ላይ የሚያምፅና ለቃልህ የማይታዘዝ ሁሉ ይገደል፤ ብቻ አንተ ጽና፤ አይዞህ፤ በርታ።”

Thai New Contemporary Bible

โยชูวา 1:1-18

องค์พระผู้เป็นเจ้า

1หลังจากโมเสสผู้รับใช้ขององค์พระผู้เป็นเจ้าสิ้นชีวิตแล้ว องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับโยชูวาบุตรนูน ผู้ช่วยของโมเสสว่า 2“โมเสสผู้รับใช้ของเราสิ้นชีวิตแล้ว บัดนี้เจ้ากับประชากรทั้งปวงจงเตรียมข้ามแม่น้ำจอร์แดน เข้าสู่ดินแดนที่เรากำลังจะยกให้ชนอิสราเอล 3ทุกแห่งที่พวกเจ้าเหยียบย่างไป เราจะยกที่แห่งนั้นให้พวกเจ้า ตามที่เราได้สัญญาไว้กับโมเสส 4ดินแดนของพวกเจ้าจะมีอาณาเขตตั้งแต่ถิ่นกันดารถึงเทือกเขาเลบานอน และจากแม่น้ำใหญ่ คือแม่น้ำยูเฟรติสจดทะเลเมดิเตอร์เรเนียนทางตะวันตก ครอบคลุมดินแดนทั้งหมดของชาวฮิตไทต์ 5ไม่มีใครยืนหยัดต่อสู้เจ้าได้ตลอดชีวิตของเจ้า เพราะเราจะอยู่กับเจ้าเหมือนที่เราอยู่กับโมเสส เราจะไม่ละจากเจ้าหรือทอดทิ้งเจ้าเลย

6“จงเข้มแข็งและกล้าหาญเถิด เพราะเจ้าจะนำประชากรเหล่านี้เข้าไปครอบครองดินแดนซึ่งเราปฏิญาณไว้กับบรรพบุรุษของพวกเขาว่าจะยกให้พวกเขา 7จงเข้มแข็งและกล้าหาญเถิด จงใส่ใจปฏิบัติตามบทบัญญัติทั้งปวงที่โมเสสผู้รับใช้ของเราให้ไว้กับเจ้า อย่าเลี่ยงไปทางซ้ายหรือทางขวา เพื่อเจ้าจะประสบความสำเร็จไม่ว่าเจ้าจะไปที่ใด 8อย่าให้หนังสือธรรมบัญญัตินี้ห่างจากปากของเจ้า จงใคร่ครวญทั้งกลางวันและกลางคืน เพื่อเจ้าจะปฏิบัติตามทุกสิ่งที่เขียนไว้อย่างเคร่งครัด แล้วเจ้าจะประสบความสำเร็จและความเจริญรุ่งเรือง 9เราสั่งเจ้าแล้วไม่ใช่หรือว่าจงเข้มแข็งและกล้าหาญเถิด อย่าหวาดกลัว อย่าท้อใจ เพราะไม่ว่าเจ้าไปที่ไหน พระยาห์เวห์พระเจ้าของเจ้าจะอยู่กับเจ้าที่นั่น”

10โยชูวาจึงสั่งบรรดาเจ้าหน้าที่ของประชาชนว่า 11“จงไปทั่วค่ายพักและแจ้งเหล่าประชากรว่า ‘จงเตรียมเสบียงอาหารให้พร้อม อีกสามวันท่านจะข้ามแม่น้ำจอร์แดนเข้าไปยึดครองดินแดน ซึ่งพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านประทานให้เป็นกรรมสิทธิ์ของท่าน’ ”

12แต่โยชูวากล่าวแก่เผ่ารูเบน เผ่ากาด และเผ่ามนัสเสห์ครึ่งเผ่าว่า 13“จงจำคำที่โมเสสผู้รับใช้ขององค์พระผู้เป็นเจ้าสั่งไว้ว่า ‘พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านประทานการพักสงบให้ท่าน และประทานดินแดนนี้แก่ท่าน’ 14ให้ภรรยา ลูกหลาน และฝูงสัตว์ของท่านพักอยู่ที่ดินแดนซึ่งโมเสสยกให้ที่ฟากตะวันออกของแม่น้ำจอร์แดนนี้ได้ แต่นักรบทั้งปวงของท่านต้องคาดอาวุธ นำพี่น้องข้ามแม่น้ำไป ท่านจงช่วยพวกพี่น้องของท่าน 15ตราบจนองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงให้พวกเขาหยุดพักเช่นเดียวกับท่าน และตราบจนพวกเขาได้ครอบครองดินแดนซึ่งพระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านจะประทานให้พวกเขาเช่นกัน หลังจากนั้นท่านจึงกลับมาครอบครองดินแดนของท่านที่ฟากตะวันออกของแม่น้ำจอร์แดนนี้ ซึ่งโมเสสผู้รับใช้ขององค์พระผู้เป็นเจ้ายกให้ท่าน”

16พวกเขาจึงตอบโยชูวาว่า “เราจะทำทุกอย่างตามที่ท่านสั่ง เราจะไปทุกแห่งที่ท่านส่งเราไป 17เราจะเชื่อฟังท่านเหมือนที่ได้เชื่อฟังโมเสสทุกประการ ขอแต่ให้พระยาห์เวห์พระเจ้าของท่านสถิตกับท่านเหมือนที่สถิตกับโมเสส 18ไม่ว่าท่านจะสั่งอะไร ใครก็ตามที่ขัดขืนและไม่เชื่อฟังคำสั่งของท่าน ผู้นั้นจะต้องตาย ขอแต่ให้ท่านเข้มแข็งและกล้าหาญเถิด!”