ኢዩኤል 3 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

ኢዩኤል 3:1-21

የተፈረደባቸው ሕዝቦች

1“በዚያ ዘመን፣ በዚያ ጊዜ፣

የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ምርኮ ስመልስ፣

2አሕዛብን ሁሉ እሰበስባለሁ፤

ወደ ኢዮሣፍጥም3፥2 ኢዮሣፍጥ፣ የስሙ ትርጕም እግዚአብሔር ይፈርዳል ማለት ነው፤ 12 ላይም እንዲሁ፤ ሸለቆ አወርዳቸዋለሁ፤

ስለ ርስቴ፣ ስለ ሕዝቤ፣ ስለ እስራኤል፣

በዚያ ልፈርድባቸው እገባለሁ፤

ምድሬን ከፋፍለዋል፤

ሕዝቤንም በሕዝቦች መካከል በታትነዋልና።

3በሕዝቤ ላይ ዕጣ ተጣጣሉ፤

ወንዶች ልጆችን በዝሙት ዐዳሪዎች ለወጡ፤

ወይን ጠጅ ለመጠጣትም፣

ሴቶች ልጆችን ሸጡ።

4“ጢሮስና ሲዶና እንዲሁም እናንተ የፍልስጥኤም ግዛቶች ሁሉ ሆይ፤ እንግዲህ በእኔ ላይ ምን አላችሁ? ስላደረግሁት ነገር ብድር ልትመልሱልኝ ነውን? የምትመልሱልኝ ከሆነ፣ በፍጥነትና በችኰላ እናንተ ያደረጋችሁትን በራሳችሁ ላይ መልሼ አደርግባችኋለሁ። 5ብሬንና ወርቄን ወስዳችኋል፤ የተመረጠውንም ንብረቴን ተሸክማችሁ ወደ ቤተ መቅደሳችሁ አስገብታችኋልና። 6ከገዛ ምድራቸው ልታርቋቸው፣ የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ሰዎች ለግሪኮች ሸጣችኋቸው።

7“እነሆ፤ እነርሱን ከሸጣችሁባቸው ቦታዎች አነሣሣቸዋለሁ፤ እናንተም ያደረጋችሁትን በገዛ ራሳችሁ ላይ እመልስባችኋለሁ። 8ወንዶችንና ሴቶች ልጆቻችሁን ለይሁዳ ሰዎች ሸጣለሁ፤ እነርሱም መልሰው በሩቅ ላሉት ለሳባ ሰዎች ይሸጧቸዋል፤” እግዚአብሔር ይህን ተናግሯልና።

9በሕዝቦች መካከል ይህን ዐውጁ፤

ለጦርነት ተዘጋጁ፤

ተዋጊዎችን አነሣሡ፤

ጦረኞችም ሁሉ ቀርበው ያጥቁ።

10ማረሻችሁ ሰይፍ፣

ማጭዳችሁም ጦር እንዲሆን ቀጥቅጡት፤

ደካማውም ሰው፣

“እኔ ብርቱ ነኝ” ይበል።

11እናንት በዙሪያ ያላችሁ ሕዝቦች ሁላችሁ፤

ፈጥናችሁ ኑ፤ በዚያም ተሰብሰቡ።

እግዚአብሔር ሆይ፤ ተዋጊዎችህን ወደዚያ አውርድ!

12“ሕዝቦች ይነሡ፤

ወደ ኢዮሣፍጥም ሸለቆ ፈጥነው ይውረዱ፤

ዙሪያውን ባሉት ሕዝቦች ሁሉ ላይ ልፈርድ፣

በዚያ እቀመጣለሁና።

13ማጭዱን ስደዱ፤

መከሩ ደርሷልና፤

ኑ ወይኑን ርገጡ፤

የወይን መጭመቂያው ሞልቶ፣

ከጕድጓዶቹም ተርፎ ፈስሷልና፤

ክፋታቸው እንደዚህ ታላቅ ነው።”

14ብዙ ሕዝብ፣ በጣም ብዙ ሕዝብ፣

ፍርድ በሚሰጥበት ሸለቆ ተሰብስቧል፤

ፍርድ በሚሰጥበት ሸለቆ፣

የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና።

15ፀሓይና ጨረቃ ይጨልማሉ፤

ከዋክብትም ከእንግዲህ አያበሩም።

16እግዚአብሔር ከጽዮን ጮኾ ይናገራል፤

ከኢየሩሳሌም ያንጐደጕዳል፤

ሰማይና ምድርም ይናወጣሉ፤

እግዚአብሔር ግን ለሕዝቡ መሸሸጊያ፣

ለእስራኤልም ልጆች መጠጊያ ይሆናል።

በረከት ለእግዚአብሔር ሕዝብ

17“ከዚያም እኔ አምላካችሁ እግዚአብሔር

በቅዱሱ ተራራዬ በጽዮን እንደምኖር ታውቃላችሁ፤

ኢየሩሳሌም የተቀደሰች ትሆናለች፤

ከእንግዲህም ወዲያ ባዕዳን አይወርሯትም።

18“በዚያ ጊዜ ተራሮች፣ አዲስ የወይን ጠጅ ያንጠባጥባሉ፤

ኰረብቶችም ወተት ያፈስሳሉ፤

በይሁዳ ያሉ ሸለቆዎች3፥18 ወይም የሸጢም ሸለቆ ሁሉ ውሃ ያጐርፋሉ፤

ከእግዚአብሔር ቤት ምንጭ ይፈልቃል፤

የሰጢምን ሸለቆ ያጠጣል።

19ግብፅ ባድማ፣

ኤዶምም ምድረ በዳ ትሆናለች፤

በምድራቸው ንጹሕ ደም በማፍሰስ፣

በይሁዳ ሕዝብ ላይ ግፍ ፈጽመዋልና።

20ይሁዳ ለዘላለም፣

ኢየሩሳሌምም ለትውልድ ሁሉ መኖሪያ ትሆናለች፤

21ደማቸውን እበቀላለሁ፤

በደለኛውንም ንጹሕ አላደርግም።”

እግዚአብሔር በጽዮን ይኖራል!

Het Boek

Joel 3:1-21

1Want zie, in die dagen en in die tijd, Waarin Ik het lot van Juda, En het lot van Jerusalem ten beste zal keren, 2Drijf Ik alle heidenen te hoop; In het Dal van Josafat zal Ik ze voeren, En daar oordeel over hen houden! Omdat ze mijn volk, en Israël mijn erfdeel, Onder de heidenen hebben verstrooid; Mijn land onder elkander verdeeld, 3En over mijn volk het lot geworpen; Den knaap hebben verruild voor een deerne, Het meisje verkocht voor wijn, om te brassen. 4Wat wilt ge van Mij, Tyrus en Sidon, En gij allen, Filistijnse gewesten? Wilt ge vergelding aan Mij oefenen, Of u wreken op Mij? Bliksemsnel stort Ik uw wraak Op uw eigen hoofd terug! 5Ge hebt mijn zilver geroofd en mijn goud, Mijn kostbaarste schatten naar uw paleizen gesleept; 6De zonen van Juda en Jerusalem Aan de Grieken verkocht, Om ze weg te voeren Ver van hun land. 7Zie, Ik roep ze op van de plaats, waarheen gij ze verkocht, Maar uw gedrag stort Ik terug op uw eigen hoofd: 8Aan de kinderen van Juda verkoop Ik uw zonen en dochters; Zij zullen ze weer aan de Sjabeërs verkopen Voor een ver verwijderd volk: Waarachtig, Jahweh heeft het gezegd! 9Kondigt het onder de heidenen af: Maakt u gereed voor de heilige strijd; Werft sterke mannen aan! Oorlogsmannen, treedt aan; rukt allen vooruit; 10Smeedt uw ploegen om tot zwaarden, Uw sikkels tot lansen! Zelfs de zwakke moet zeggen: Ik ben een held! 11Vooruit, gij allen, u gehaast, Omliggende volken, Sluit de rangen aaneen: Jahweh, breng daar uw strijders bijeen! 12Op heidenen; op naar het Dal van Josafat; Want daar zit Ik ten oordeel over alle omliggende volken! 13Slaat de sikkel erin, want de oogst is rijp, Gaat treden, want de perskuip is vol; De bakken vloeien over, Want hun boosheid is groot! 14Drommen, drommen in het Dal der Beslissing; Want Jahweh’s dag is nabij in het Dal der Beslissing! 15Zon en maan verduisteren, De sterren trekken haar glans terug; 16Jahweh buldert uit Sion, dondert uit Jerusalem: Hemel en aarde beven ervan! Maar voor zijn volk is Jahweh een toevlucht, Een burcht voor Israëls zonen. 17Dan zult ge weten, dat Ik, Jahweh, uw God ben, Dat Ik woon op de Sion, mijn heilige berg; Dan zal Jerusalem heilig wezen, Geen vreemdeling komt er meer in! 18Op die dag druipen de bergen van wijn, Vloeien de heuvelen van melk, En al de beken van Juda Stromen over van water. Een bron zal uit het huis van Jahweh ontspringen, En zelfs het Sjittim-dal besproeien! 19Egypte zal een steppe worden, Edom een dorre woestijn; Omdat ze Juda’s kinderen hebben mishandeld, Onschuldig bloed in hun land hebben vergoten. 20Maar Juda zal in eeuwigheid blijven bestaan, Jerusalem van geslacht tot geslacht; 21hun bloed laat Ik niet ongewroken: Ik, Jahweh, blijf wonen op Sion!