ኢሳይያስ 7 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 7:1-25

የዐማኑኤል ምልክትነት

1የዖዝያን የልጅ ልጅ፣ የኢዮአታም ልጅ አካዝ የይሁዳ ንጉሥ በነበረበት ዘመን፣ የሶርያ ንጉሥ ረአሶንና የእስራኤል ንጉሥ የሮሜልዩ ልጅ ፋቁሔ ኢየሩሳሌምን ሊወጉ ወጡ፤ ነገር ግን ድል ሊያደርጓት አልቻሉም።

2ለዳዊት ቤት፣ “ሶርያና ኤፍሬም ተባብረዋል” የሚል ወሬ በደረሰ ጊዜ፣ የዱር ዛፍ በነፋስ እንደሚናወጥ የአካዝና የሕዝቡ ልብ እንዲሁ ተናወጠ።

3እግዚአብሔርም ኢሳይያስን እንዲህ አለው፤ “አንተና ልጅህ ሸአር ያሹብ7፥3 ሸአር ያሹብ ማለት፣ ቅሬታዎች ይመለሳሉ ማለት ነው። አካዝን ለመገናኘት ወደ ልብስ ዐጣቢው ዕርሻ በሚወስደው መንገድ ወዳለው ወደ ላይኛው የኵሬ መስኖ ጫፍ ውጡ፤ 4እንዲህም በለው፤ ‘ተጠንቀቅ፤ ተረጋጋ፤ አትፍራ፤ በእነዚህ ከእሳት ተርፈው በሚጤሱት በሁለቱ የዕንጨት ጕማጆች፣ በሶርያና በንጉሥዋ በረአሶን እንዲሁም በሮሜልዩ ልጅ ቍጣ አትሸበር። 5ሶርያ ኤፍሬምና፣ የሮሜልዩ ልጅ ሊያጠፉህ እንዲህ ብለው ተማከሩ፤ 6“ይሁዳን እንውረር፤ እንበታትነው፤ ተከፋፍለንም እንግዛው፤ የጣብኤልንም ልጅ እናንግሥባት።” 7ጌታ እግዚአብሔር ግን እንዲህ ይላል፤

“ ‘ይህ ምክራቸው አይፈጸምም፤

ከቶም አይደረግም፤

8የሶርያ ራስ ደማስቆ፣

የደማስቆ ራስ ረአሶን ነውና፤

በስድሳ አምስት ዓመት ውስጥ፣

የኤፍሬም ሕዝብ ይበታተናል፤ ሕዝብ መሆኑም ይቀራል።

9የኤፍሬም ራስ ሰማርያ፣

የሰማርያም ራስ የሮሜልዩ ልጅ ነው።

እንግዲህ በእምነታችሁ ካልጸናችሁ፣

ፈጽሞ መቆም አትችሉም።’ ”

10እንደ ገናም እግዚአብሔር አካዝን እንዲህ አለው፤ 11“ከጥልቁ ጥልቅ ወይም ከከፍታው ከፍታ ምልክት እንዲሰጥህ ከእግዚአብሔር ከአምላክህ ለምን።”

12አካዝ ግን፣ “አልለምንም፣ እግዚአብሔርንም አልፈታተንም” አለ።

13ኢሳይያስም እንዲህ አለ፤ “እናንተ የዳዊት ቤት ሆይ፤ ስሙ፤ የሰውን ትዕግሥት መፈታተናችሁ አንሶ የአምላኬን ትዕግሥት ትፈታተናላችሁን? 14ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፤ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፤ ስሙንም ዐማኑኤል7፥14 ዐማኑኤል ማለት፣ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው። ብላ ትጠራዋለች። 15ክፉውን መተውና መልካሙን መምረጥ ሲችል ቅቤና ማር ይበላል። 16ነገር ግን ሕፃኑ ክፉውን መተውና መልካሙን መምረጥ ከመቻሉ በፊት የፈራሃቸው የሁለቱ ነገሥታት ምድር ባድማ ይሆናል። 17ኤፍሬም ከይሁዳ ከተለየበት ቀን ጀምሮ እግዚአብሔር ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ዘመን በአንተ፣ በሕዝብህና በአባትህ ቤት ላይ ያመጣል፤ የሚያመጣውም የአሦርን ንጉሥ ነው።”

18በዚያን ቀን እግዚአብሔር ራቅ ካሉት ከግብፅ ወንዞች ዝንቦችን፣ ከአሦርም ምድር ንቦችን በፉጨት ይጠራል። 19እነርሱም በሙሉ መጥተው፣ በየበረሓው ሸለቆ፣ በየዐለቱ ንቃቃት፣ በየእሾኹ ቍጥቋጦና በየውሃው ጕድጓድ ሁሉ ይሰፍራሉ። 20በዚያን ቀን፣ እግዚአብሔር ከወንዝ7፥20 የኤፍራጥስ ወንዝ ነው። ማዶ በተከራየው ምላጭ፣ ማለትም በአሦር ንጉሥ፣ የራስና የእግር ጠጕራችሁን እንዲሁም ጢማችሁን ይላጫል። 21በዚያን ቀን፣ አንድ ሰው አንዲት ጊደርና ሁለት በግ ብቻ ይተርፈዋል። 22ከሚሰጡትም የተትረፈረፈ ወተት ቅቤ ይበላል፤ በምድሪቱም የቀሩ ሁሉ ቅቤና ማር ይበላሉ። 23በዚያን ቀን ሺሕ ሰቅል7፥23 11.5 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ብር የሚያወጣ አንድ ሺሕ የወይን ተክል የነበረበት ቦታ ሁሉ፣ ኵርንችትና እሾኽ ብቻ ይሆናል። 24ምድሪቱ በኵርንችትና በእሾኽ ስለምትሸፈን፣ ሰዎች ወደዚያ የሚገቡት ቀስትና ፍላጻ ይዘው ነው፤ 25ኵርንችትና እሾኹን በመፍራት ከዚህ በፊት በመቈፈሪያ ተቈፍረው ወደ ነበሩት ወደ እነዚያ ኰረብታዎች ሁሉ ከእንግዲህ አትሄድም፤ ነገር ግን የከብቶች መሰማሪያና የበጎች መፈንጫ ቦታ ይሆናሉ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

以赛亚书 7:1-25

给亚哈斯王的信息

1乌西雅的孙子、约坦的儿子亚哈斯犹大王时,亚兰利迅利玛利的儿子以色列比加来攻打耶路撒冷,却无法攻破。 2亚兰以色列结盟的消息传到犹大王那里,举国上下都吓得胆战心惊,好像林中被风吹动的树木。 3耶和华对以赛亚说:“你带着儿子施亚雅述出去,到上池水沟的尽头——通往漂布场的路上迎见亚哈斯4告诉他要谨慎镇定,不要害怕,不要因亚兰利迅利玛利的儿子的怒气而胆怯,他们不过是两个冒烟的火把头。 5亚兰王和以法莲利玛利的儿子阴谋毁灭他, 6企图攻打并瓜分犹大,改立他比勒的儿子为王。 7但主耶和华说,

“‘这阴谋必无法得逞。

8亚兰的都城是大马士革

大马士革的首领是利迅

六十五年之内,

以色列必亡国。

9以色列的都城是撒玛利亚

撒玛利亚的首领是利玛利的儿子。

你们信心若不坚定,

必无法坚立。’”

10耶和华又对亚哈斯说: 11“向你的上帝耶和华求个征兆吧,或显在天上,或显在阴间。” 12亚哈斯说:“我不求,我不要试探耶和华。” 13以赛亚说:“大卫的子孙啊,你们听着!你们使人厌烦还不够吗?还要使我的上帝厌烦吗? 14所以,主会亲自给你们一个征兆,必有童贞女7:14 童贞女”或译“女子”。怀孕生子并给祂取名叫以马内利7:14 以马内利”意思是“上帝与我们同在”。15他将吃奶酪和蜂蜜,一直到他能明辨是非。 16然而,在他能明辨是非之前,你所惧怕的这二王的国土必荒废。

17“之后,耶和华必让亚述王来攻击你们。这是你全家及你的人民自以色列犹大分裂以来从未有的日子。 18那时,耶和华的哨声一响,埃及的大军必像苍蝇一样从遥远的尼罗河飞扑而来,亚述的人马必如黄蜂一样蜂拥而至, 19遍布险峻的山谷、岩穴、一切荆棘丛和草场。 20那时,主必使用幼发拉底河对岸的亚述王来毁灭你们,就像用租来的剃刀剃光你们的头发、胡须和身上的汗毛。

21“那时,一个人将养活一头母牛和两只羊。 22因出产的奶丰富,他就有奶酪吃,境内剩下的人都将吃奶酪和蜂蜜。 23那时,本来有千株葡萄、价值千金的园子必长满荆棘和蒺藜, 24人们必带着弓箭去打猎,因为遍地长满了荆棘和蒺藜。 25你因惧怕荆棘和蒺藜,将不再去从前用锄头开垦的山地,那里将成为牧放牛羊的地方。”