ኢሳይያስ 29 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 29:1-24

ወዮ ለዳዊት ከተማ

1ዳዊት የሰፈረብሽ ከተማ፣

አርኤል፣ አርኤል ወዮልሽ!

ዓመት በዓመት ላይ ጨምሪ፣

ዐውደ ዓመትሽም ይቀጥል።

2ነገር ግን አርኤልን29፥2 በዕብራይስጡ፣ የመሠዊያ መሬት የሚለው ቃል ድምፀት፣ አርኤል ከሚለው ቃል ጋር አንድ ዐይነት ነው። እከብባለሁ፤

ታለቅሳለች፤ ዋይ ዋይ ትላለች፤

ለእኔም እንደ መሠዊያ ስፍራ ትሆንልኛለች።

3በዙሪያሽ እሰፍራለሁ፤

በቅጥር እከብብሻለሁ፤

የከበባ ዐምባም ሠርቼ አስጨንቅሻለሁ።

4ወደ ታች ትወርጃለሽ፤ ከምድርም በታች ትናገሪያለሽ፤

ንግግርሽ ከትቢያ እየተጕተመተመ ይወጣል፤

ድምፅሽ እንደ መናፍስት ድምፅ ከመሬት ወደ ላይ ይመጣል፤

ንግግርሽ ከትቢያ ያንሾካሹካል።

5ነገር ግን ብዙ ጠላቶችሽ እንደ ትቢያ ብናኝ፣

የጨካኞች መንጋ በነፋስ እንደሚነዳ

ገለባ ይሆናሉ።

ድንገት ሳይታሰብም፣

6የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በነጐድጓድ፣ በምድር መናወጥና በታላቅ ድምፅ፣

በዐውሎ ነፋስና በኀይለኛ ሞገድ፣ ፈጽሞ በሚባላም የእሳት ነበልባል ይመጣል።

7አርኤልን የሚወጋ የአሕዛብ ሁሉ መንጋ፣

በእርሷና በምሽጓ ላይ አደጋ የሚጥልና የሚከብባት፣

እንደ ሕልም

በሌሊትም እንደሚታይ ራእይ ይሆናል።

8የተራበ ሰው በሕልሙ ሲበላ ዐድሮ፣

ነገር ግን ሲነቃ ራቡ እንዳልለቀቀው፣

የጠማውም ሰው በሕልሙ ሲጠጣ ዐድሮ፣

ነገር ግን ሲነቃ እንደ ዛለና ጥማቱም እንዳልተወው፣

የጽዮንን ተራራ የሚወጋ፣

የአሕዛብ መንጋ ሁሉ እንዲሁ ይሆናል።

9ነኹልሉ ተደነቁም፤

ተጨፈኑ፤ እስከ ወዲያኛውም ታውራችሁ ቅሩ፤

በወይን ጠጅ አይሁን እንጂ ስከሩ፤

በሚያሰክር መጠጥ አይሁን እንጂ ተንገዳገዱ።

10እግዚአብሔር ከባድ እንቅልፍ ጥሎባችኋል፤

ዐይኖቻችሁን፣ ነቢያትን ጨፍኖባችኋል፤

ራሶቻችሁን፣ ባለ ራእዮችን ሸፍኖባችኋል።

11ይህ ሁሉ ራእይ በጥቅልል መጽሐፍ ውስጥ እንደ ታሸገ ቃል ሆኖባችኋል። ጥቅልሉንም መጽሐፍ ማንበብ ለሚችል ሰው፣ “እባክህ አንብብልን” ብላችሁ ብትሰጡት፣ “ታሽጓልና አልችልም” ይላችኋል። 12ደግሞም ጥቅልሉን መጽሐፍ ማንበብ ለማይችል ሰው፣ “እባክህን አንብብልን” ብላችሁ ብትሰጡ፣ “ማንበብ አልችልም” ይላችኋል።

13እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ይህ ሕዝብ በአፉ ወደ እኔ ይቀርባል፤

በከንፈሩም ያከብረኛል፤

ልቡ ግን ከእኔ የራቀ ነው፤

የሚያመልከኝም፣

ሰው ባስተማረው ሰው ሠራሽ ሥርዐት ብቻ ነው29፥13 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን፣ በከንቱ ያመልኩኛል፤ ትምህርታቸው ሰው ያሰተማረው ሰው ሠራሽ ሥርዐት ብቻ ነው ይላል።

14ስለዚህ ይህን ሕዝብ በድንቅ ላይ ድንቅ

ነገር እያደረግሁ፣

ዳግመኛ አስገርመዋለሁ፤

የጥበበኞች ጥበብ ይጠፋል፤

የአስተዋዮችም ማስተዋል ይበንናል።”

15ሐሳባቸውን ከእግዚአብሔር ለመደበቅ፣

ወደ ጥልቅ ጕድጓድ ለሚወርዱ

ሥራቸውንም በጨለማ ለሚያከናውኑ፣

“ማን ያየናል? ማንስ ያውቅብናል” ለሚሉ ወዮላቸው!

16እናንተ ነገሮችን ትገለብጣላችሁ

ሸክላ ሠሪውን እንደ ሸክላ ትመለከታላችሁ፤

ለመሆኑ፣ ተሠሪ ሠሪውን፣

“እርሱ አልሠራኝም” ይለዋልን?

ሸክላ የሠራውን፣

“እርሱ ምንም አያውቅም” ይለዋልን?

17ሊባኖስ ወደ ለም ዕርሻነት ለመለወጥ፣

ለም የሆነውም መሬት ወደ ዱርነት ለመለወጥ ጥቂት ጊዜ አልቀረውምን?

18በዚያን ጊዜ ደንቈሮ የጥቅልሉን መጽሐፍ ቃል ይሰማል፤

የዐይነ ስውሩም ዐይኖች

ከጭጋግና ከጨለማ ተላቀው ያያሉ።

19ትሑታን በእግዚአብሔር

ምስኪኖችም በእስራኤል ቅዱስ እንደ ገና ሐሤት ያደርጋሉ።

20ጨካኞች እንዳልነበሩ ይሆናሉ፤

ፌዘኞችም በንነው ይጠፋሉ፤

ለክፋት ያደፈጡ ሁሉ ይወገዳሉ።

21ሰውን በነገር በደለኛ የሚያደርጉ፣

በተከሳሽ ላይ ወጥመድ የሚዘረጉ፣

በሐሰት ምስክር ፍትሕን ከንጹሓን የሚቀሙ ይቈረጣሉ።

22ስለዚህ አብርሃምን የተቤዠው እግዚአብሔር

ለያዕቆብ ቤት እንዲህ ይላል፤

“ያዕቆብ ከእንግዲህ ወዲያ አያፍርም፤

ፊቱም ከእንግዲህ አይለዋወጥም።

23በመካከላቸው የእጄ ሥራ የሆኑ፣

ልጆቻቸውን ሲያዩ፣

ስሜን ይቀድሳሉ፤

የያዕቆብን ቅዱስ ቅድስና ያውቃሉ፤

በእስራኤልም አምላክ ፊት በፍርሀት ይቆማሉ።

24በመንፈስ የሳቱ ያስተውላሉ፤

የሚያጕረመርሙም ምክር ይቀበላሉ።”

Japanese Contemporary Bible

イザヤ書 29:1-24

29

ダビデの町への叱責

1「ああ、ダビデの町エルサレムよ、

おまえは大きな災難に会う。

年ごとに、おまえは多くの供え物をささげる。

2しかし、わたしが重い罰を加えるので、

泣き声と悲しみがあふれる。

「アリエル」というあだ名のとおり、エルサレムは血だらけの祭壇になるからだ。

3わたしはおまえの敵となる。

エルサレムを包囲し、攻めたて、

周囲に要塞を築いて滅ぼす。

4おまえの声は、埋められた地中から、

幽霊のようにかすかに聞こえるばかりだ。

5だが残酷な敵も、あっという間に

もみがらのように吹き飛ばされる。

6天の軍勢の主であるわたしは、雷と地震とつむじ風、

火をもって不意に彼らに襲いかかる。

7エルサレムに戦いをいどむ国はすべて、

一夜の夢のように消え去る。

8空腹の人が食事の夢を見ても

変わらず空腹であるように、

また、のどの渇いた人が水を飲む夢を見ても

変わらず渇きで苦しむように、

敵は勝利の夢を見るが、現実とはならない。」

9あなたがたは信じられないのですか。

信じたくないのなら、かってに行動し、

見えない目で進んで行きなさい。

あなたがたは頭の働きが鈍くなりますが、

ぶどう酒に酔ったせいではありません。

足がふらつきますが、強い酒のせいではありません。

10主が深い眠りの霊を注いだからです。

主が預言者や先見者の目をふさいだので、

11将来の出来事のいっさいは、彼らにとって封をされた書物同然になりました。ですから、いくら読解力のある人に渡しても、「読めません。封がしてありますから」と答えます。 12別の人に回すと、「残念ながら、私は文字を読むことができません」という返事です。

13そこで主は語ります。

「この民は、口先ではわたしの民だと言いながら、

実際にはわたしに従っていない。

彼らの礼拝は、機械的に覚えた文句の反復にすぎない。

14もう黙ってはいられない。

偽善者どもに思い知らせよう。

最高の知恵さえ、愚か者同然にしてしまおう。」

15ああ、自分の計画を神に隠そうとする者、

陰で悪を行う者。

彼らは言います。

「神はこんなところまで目が届かない。

ここで何が起こっているかなど、

知っているわけがない。」

16なんと愚かなことを言うのでしょう。

陶器師である神は、陶器にすぎないあなたがたより

偉くないのでしょうか。

あなたは神に向かって、

「あなたは私を造らなかった」と反抗するのですか。

機械がその考案者に、「あなたを解雇する」

と言うでしょうか。

17もうしばらくすると、レバノンの荒野は

再び実り豊かな平野となり、

樹木が茂るよく肥えた森となります。

18その日、耳の聞こえない人が書物のことばを聞き、

盲人は暗闇ごしに神の計画したことを見ます。

19柔和な人は主からくる新しい喜びにあふれ、

貧しい人はイスラエルのきよい神によって

喜び踊ります。

20弱い者をしいたげる者はいなくなり、

あざける者は断たれ、

悪事を企む者は一人残らず殺されます。

21そういう者たちは、

ほんの少しのことにも言いがかりをつけては

けんかを売り、裁判になれば、

有罪の判決を下した裁判官を待ちぶせて

袋だたきにします。

あらゆる口実をもうけて不正を行うのです。

22それゆえ、アブラハムを贖い出した主は、

こう語ります。

「わたしの民は恐れのあまり青ざめたり、

恥じ入ったりしない。

23人口が急増し、経済が発展するのを見て、

わたしの名を恐れ、わたしをたたえるようになる。

24間違いを犯していた者は真理を信じ、

不平ばかり言っていた者は、

進んで教えを受けるようになる。」