ኢሳይያስ 27 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 27:1-13

የእስራኤል ዐርነት መውጣት

1በዚያ ቀን እግዚአብሔር

ተወርዋሪውን እባብ ሌዋታንን፣

የሚጠቀለለውን ዘንዶ ሌዋታንን

በብርቱ፣ በታላቁና በኀይለኛ ሰይፍ ይቀጣዋል፤

የባሕሩንም ግዙፍ አውሬ ይቈራርጠዋል።

2በዚያን ቀን እንዲህ ይባላል፤

“ለመልካሙ የወይን ቦታ ዘምሩለት፤

3እኔ እግዚአብሔር ጠባቂው ነኝ፤

ዘወትር ውሃ አጠጣዋለሁ፤

ስለዚህ ማንም አይጐዳውም፣

ቀንና ሌሊት እጠብቀዋለሁ፤

4እኔ አልቈጣም።

እሾኽና ኵርንችት ምነው በተነሡብኝ!

ለውጊያ በወጣሁባቸው፣

አንድ ላይ ባቃጠልኋቸው!

5አለዚያ ይምጡና መሸሸጊያቸው ያድርጉኝ፤

ከእኔ ጋር ሰላም ይፍጠሩ፤

አዎን፤ ከእኔ ጋር ሰላም ያድርጉ።”

6በሚመጡት ቀናት ያዕቆብ ሥር ይሰድዳል፤

እስራኤልም ያቈጠቍጣል፣ ያብባልም፤

በፍሬያቸውም ምድርን ሁሉ ይሞላሉ።

7የመቷትን እንደ መታቸው፣

እግዚአብሔር እርሷንስ መታትን?

የገደሏትን እንደ ገደላቸው፣

እርሷስ ተገደለችን?

8በጦርነትና በስደት ተፋለምሃት27፥8 በዕብራይስጡ የዚህ ሐረግ ትርጕም በትክክል አይታወቅም።

የምሥራቅ ነፋስ እንደሚነፍስበት ቀን፣

በብርቱ ዐውሎ ነፋስ አሳደድሃት።

9ያዕቆብ የመሠዊያ ድንጋዮችን፣

እንደ ኖራ ድንጋይ ፈጭቶ ሲያደቅቃቸው፣

የአሼራን ዐምድና የዕጣን መሠዊያዎችን፣

ከቦታቸው ነቅሎ ሲጥል፣

በዚያን ጊዜ በደሉ ይሰረይለታል፤

ይህም ኀጢአቱን የማስወገዱ ሙሉ ፍሬ ይሆናል።

10የተመሸገባት ከተማ ባዶዋን ቀርታለች፤

እንደ ምድረ በዳም የተተወች ስፍራ ሆናለች፤

ጥጆች በዚያ ይሰማራሉ፤

እዚያም ይተኛሉ፤

ቅርንጫፎቿንም ልጠው ይበላሉ።

11ጫፎቿ ሲደርቁ ይሰበራሉ፤

ሴቶችም መጥተው ይማግዷቸዋል።

ማስተዋል የሌለው ሕዝብ ስለሆነ፣

ፈጣሪው አይራራለትም፤

ያበጀውም አይምረውም።

12በዚያ ቀን ከኤፍራጥስ ወንዝ አንሥቶ እስከ ግብፅ ደረቅ ወንዝ፣ እግዚአብሔር እህሉን ይወቃል፤ እናንተም የእስራኤል ልጆች ሆይ፤ አንድ በአንድ ትሰበሰባላችሁ። 13በዚያ ቀን ታላቅ መለከት ይነፋል፤ በአሦር የጠፉትና በግብፅ የተሰደዱትም መጥተው፣ በተቀደሰው ተራራ በኢየሩሳሌም እግዚአብሔርን ያመልካሉ።

Thai New Contemporary Bible

อิสยาห์ 27:1-13

การกอบกู้อิสราเอล

1ในวันนั้น

องค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงใช้พระแสงดาบ อันยิ่งใหญ่และทรงอานุภาพลงโทษเลวีอาธาน

เจ้าพญานาคที่เลื้อยปราดอย่างรวดเร็ว

เจ้างูใหญ่ที่ขดตัวอยู่

พระองค์จะทรงสังหารเจ้าสัตว์ร้ายมหึมาแห่งท้องทะเล

2ในวันนั้น

“จงร้องเพลงเกี่ยวกับสวนองุ่นที่มีผลดกดังนี้ว่า

3เราผู้เป็นองค์พระผู้เป็นเจ้าดูแลสวนนั้น

เรารดน้ำให้ตลอดเวลา

เฝ้าดูทั้งวันทั้งคืน

ไม่ยอมให้ใครมาทำอันตราย

4เราไม่โกรธ

แต่ถ้ามีหนามใหญ่น้อยออกมาให้เห็น!

เราจะไปรบรากับมัน

และเผามันทิ้ง

5หรือไม่ก็ให้มันมาพักพิงเรา

ให้มาเจรจาสันติภาพกับเรา

ให้มาเจรจาสันติภาพกับเรา”

6ในภายภาคหน้ายาโคบจะหยั่งราก

อิสราเอลจะผลิตาและผลิดอกบาน

และออกผลทั่วโลก

7พระองค์ทรงลงโทษอิสราเอล

เหมือนที่ทรงลงโทษศัตรูของเขาหรือ?

อิสราเอลถูกฆ่า

เหมือนคนที่ฆ่าอิสราเอลถูกฆ่าหรือ?

8พระองค์ทรงลงโทษอิสราเอลด้วยสงคราม27:8 ในภาษาฮีบรูคำนี้มีความหมายไม่ชัดเจนและการเนรเทศ

ทรงขับไล่เขาออกไปด้วยความเกรี้ยวกราด

เหมือนวันที่ลมตะวันออกพัด

9โดยการนี้ ความผิดของยาโคบจะได้รับการลบล้างไป

และนี่จะเป็นการกำจัดบาปของเขาอย่างสิ้นเชิง

พระองค์ทรงทำให้หินแท่นบูชา

เป็นเหมือนหินชอล์กที่ถูกบดละเอียด

ไม่มีเสาเจ้าแม่อาเชราห์27:9 คือ สัญลักษณ์ของเจ้าแม่อาเชราห์หรือแท่นเครื่องหอม

เหลืออยู่อีกเลย

10เมืองป้อมปราการก็ตั้งอยู่อย่างโดดเดี่ยว

ถูกทิ้งร้างว่างเปล่าเหมือนถิ่นกันดาร

วัวกินหญ้าอยู่ที่นั่น

มันเอนตัวลง

เคี้ยวกิ่งไม้จนโล่งเตียน

11เมื่อง่ามไม้แห้ง มันก็หัก

พวกผู้หญิงก็มาเก็บไปทำฟืน

เพราะชนชาตินี้ไม่มีความเข้าใจ

ฉะนั้นพระผู้สร้างของพวกเขาจึงไม่เอ็นดูสงสารเขา

พระองค์ผู้ทรงสร้างพวกเขาไม่แสดงความโปรดปรานต่อพวกเขา

12ในวันนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงนวดเอาข้าวตั้งแต่แม่น้ำยูเฟรติสถึงลำน้ำแห่งอียิปต์ และชนชาติอิสราเอลเอ๋ย ท่านจะถูกรวบรวมมาทีละคนๆ 13ในวันนั้นจะมีการเป่าแตรใหญ่ หลายคนที่กำลังจะพินาศในอัสซีเรียและผู้ที่ถูกเนรเทศไปอียิปต์จะกลับมานมัสการองค์พระผู้เป็นเจ้าบนภูเขาศักดิ์สิทธิ์ในเยรูซาเล็ม