ኢሳይያስ 19 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 19:1-25

ስለ ግብፅ የተነገረ ትንቢት

1ስለ ግብፅ የተነገረ ንግር፤

እነሆ፤ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ላይ ተቀምጦ

ወደ ግብፅ ይመጣል፤

የግብፅ ጣዖቶች በፊቱ ይርዳሉ፤

የግብፃውያንም ልብ በውስጣቸው ይቀልጣል።

2“ግብፃዊውን በግብፃዊው ላይ አስነሣለሁ፤

ወንድም ወንድሙን፣

ባልንጀራ ባልንጀራውን፣

ከተማም ከተማን፣

መንግሥትም መንግሥትን ይወጋል።

3የግብፃውያን ልብ ይሰለባል፤

ዕቅዳቸውንም መና አስቀራለሁ፤

እነርሱም ጣዖታትንና የሙታንን መናፍስት፣

መናፍስት ጠሪዎችንና ጠንቋዮችን ምክር ይጠይቃሉ።

4ግብፃውያንን አሳልፌ

ለጨካኝ ጌታ ክንድ እሰጣቸዋለሁ፤

አስፈሪ ንጉሥም ይገዛቸዋል”

ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

5የአባይ ወንዝ ይቀንሳል፤

ውሃውም እየጐደለ ይሄዳል።

6መስኖዎቹ ይከረፋሉ፤

የግብፅ ጅረቶች ይጐድላሉ፤ ይጠፋሉም።

ደንገሉና ቄጠማውም ይጠወልጋል፤

7እንዲሁም በአባይ ዳር፣

በወንዙ መፋሰሻ ላይ ያሉት ተክሎች ይጠወልጋሉ።

በአባይ ዳር የተዘራው ዕርሻ ሁሉ፣

በነፋስ ይወሰዳል፤ ምንም አይቀርም።

8ዓሣ አጥማጆች ያዝናሉ፤

በአባይ ወንዝ ላይ መንጠቋቸውን የሚወረውሩ ሁሉ ያለቅሳሉ፤

በውሃ ላይ መረባቸውን የሚጥሉ ሁሉ፣

ጕልበታቸው ይዝላል።

9የተነደፈ የተልባ እግር የሚፈትሉ፣

የተባዘተ ጥጥ የሚሠሩ ሸማኔዎችም ተስፋ ይቈርጣሉ።

10ልብስ ሠሪዎች ያዝናሉ፤

ደመወዝተኞችም ልባቸው ይሰበራል።

11የጣኔዎስ አለቆች በጣም ሞኞች ናቸው፤

የፈርዖን ጠቢባን ምክራቸው የማይረባ ነው፤

ፈርዖንን፣ “እኔ ከጥበበኞች አንዱ ነኝ፤

የጥንት ነገሥታትም ደቀ መዝሙር ነኝ”

እንዴት ትሉታላችሁ?

12የእናንተ ጠቢባን አሁን የት አሉ?

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በግብፅ ላይ ያሰበውን ነገር፣

እስቲ ያሳዩአችሁ፤ ያሳውቋችሁም።

13የጣኔዎስ አለቆች ተሞኝተዋል፤

የሜምፊስ ሹማምት ተታልለዋል፤

የሕዝቧ ዋና ዋናዎች፣

ግብፅን አስተዋታል።

14እግዚአብሔር የድንዛዜን መንፈስ አፍስሶባቸዋል፤

ሰካራም በትፋቱ ዙሪያ እንደሚንገዳገድ፣

ግብፅንም በምታደርገው ነገር ሁሉ

እንድትንገዳገድ አደረጓት።

15ራስም ይሁን ጅራት፣ የዘንባባ ዝንጣፊም ይሁን ደንገል፣

ለግብፅ የሚያደርጉላት አንዳች ነገር የለም።

16በዚያን ቀን ግብፃውያን እንደ ሴት ይሆናሉ፤ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ ካነሣው ክንዱ የተነሣ በፍርሀት ይንቀጠቀጣሉ። 17የይሁዳ ምድር በግብፅ ላይ ሽብር ትነዛለች፤ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ ካቀደው የተነሣ፣ ስለ ይሁዳ ወሬ የሰማ ሁሉ ይሸበራል።

18በዚያ ቀን አምስት የግብፅ ከተሞች በከነዓን ቋንቋ ይናገራሉ፤ የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርም ወገን ለመሆን ቃል ኪዳን ይገባሉ፤ ከእነዚህም ከተሞች አንዲቱ የጥፋት ከተማ ተብላ ትጠራለች።

19በዚያ ቀን በግብፅ ምድር መካከል ለእግዚአብሔር መሠዊያ ይሠራል፤ በድንበሯም ላይ ለእግዚአብሔር ዐምድ ይቆማል። 20ይህም በግብፅ ምድር ለሰራዊት ጌታ ለእግዚአብሔር ምልክትና ምስክር ይሆናል፤ ከሚያስጨንቋቸውም የተነሣ ወደ እግዚአብሔር ሲጮኹ፣ አዳኝና ታዳጊ ይልክላቸዋል፤ እርሱም ያድናቸዋል። 21እግዚአብሔር ራሱን ለግብፃውያን ይገልጣል፤ እነርሱም በዚያ ቀን እግዚአብሔርን ያውቁታል፤ በመሥዋዕትና በእህል ቍርባንም ያመልኩታል። ለእግዚአብሔር ስለት ይሳላሉ፤ የተሳሉትንም ይፈጽሙታል። 22እግዚአብሔር ግብፅን በመቅሠፍት ይመታታል፤ መትቶም፤ ይፈውሳቸዋል። እነርሱም ወደ እግዚአብሔር ይመለሳሉ፤ እርሱም ልመናቸውን ሰምቶ ይፈውሳቸዋል።

23በዚያ ቀን ከግብፅ ወደ አሦር አውራ መንገድ ይዘረጋል፤ አሦራውያን ወደ ግብፅ፣ ግብፃውያንም ወደ አሦር ይሄዳሉ፤ ግብፃውያንና አሦራውያን በአንድነት ያመልካሉ። 24በዚያ ቀን እስራኤል፣ ከግብፅና ከአሦር ጋር የምድር በረከት ለመሆን በሦስተኛነት ትቈጠራለች። 25የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርም፣ “ሕዝቤ ግብፅ፣ የእጄ ሥራ አሦር፣ ርስቴም እስራኤል የተባረኩ ይሁኑ” ብሎ ይባርካቸዋል።

Het Boek

Jesaja 19:1-25

1Godsspraak over Egypte. Zie, Jahweh bestijgt een vlugge wolk, En rijdt Egypteland binnen: Egypte’s goden beven voor Hem, Het hart van Egypte smelt weg in zijn borst. 2Ik hits Egypte op tegen Egypte, Ze vechten tegen elkander: Vriend tegen vriend, en stad tegen stad, En rijk tegen rijk! 3Egypte verliest zijn bezinning, Zijn plannen gooi Ik dooreen; Ze vragen hun goden en bezweerders om raad, Hun schimmen en waarzeggers. 4Maar Ik lever Egypte over aan een grimmigen meester, Een wrede koning zal over hen heersen: Is de godsspraak des Heren, Van Jahweh der heirscharen! 5De wateren der zee zinken weg, De stroom wordt leeg en droogt uit, 6De kanalen worden moerassen, De Nijlarmen van Egypte verzanden, staan droog. Riet en bies verwelken, 7Met het oevergras langs de Nijl; En al wat de Nijl deed ontkiemen, Verdort, verwaait en verdwijnt. 8De vissers klagen en treuren, Allen, die in de Nijl komen hengelen; En die de netten werpen, Zitten aan het water te kwijnen. 9De vlasbewerkers staan verlegen, Spinsters en kammers bleek van ontzetting, 10De wevers verslagen, Alle loonarbeiders onthutst. 11Enkel dwazen zijn de vorsten van Sóan, Farao’s wijzen een domme raad; Hoe durft ge nog tot Farao zeggen: Ik ben een zoon der wijzen, der oude vorsten? 12Waar, waar blijven uw wijzen? Laten ze u toch eens zeggen en melden, Wat Jahweh der heirscharen Over Egypte besloot! 13Verdwaasd staan de vorsten van Sóan, Verbijsterd de vorsten van Nof, De stamhoofden sleuren Egypte maar rond, 14Want Jahweh heeft ze duizelig gemaakt. Ze laten Egypte tasten bij al wat het doet, Zoals een dronkaard in zijn uitbraaksel tuimelt; 15Geen enkel werk komt in Egypte tot stand, Van kop of staart, van palmtak of riet. 16Op die dag zal Egypteland Sidderen en beven als vrouwen: Voor de dreigende hand van Jahweh der heirscharen, Die Hij tegen hem opheft. 17En Juda’s bodem zal een verschrikking zijn voor Egypte; Het beeft al, wanneer er maar iemand van spreekt: Om het raadsbesluit van Jahweh der heirscharen, Dat Hij over hen heeft gewezen. 18Maar eens zullen er vijf steden zijn in het land van Egypte, Die Kanaäns taal zullen spreken, En aan Jahweh der heirscharen trouw zullen zweren: En één er van zal Zonnestad heten. 19Op die dag zal een altaar voor Jahweh staan Midden in het land van Egypte, En op zijn grenzen een zuil Ter ere van Jahweh! 20Dit zal een teken zijn en getuige Voor Jahweh der heirscharen in het land van Egypte: Wanneer ze dan tot Jahweh roepen om hun verdrukkers, Zal Hij hun een Verlosser zenden, een Wreker, die hen zal redden. 21Zo zal Jahweh zich aan Egypte openbaren, En Egypte Jahweh erkennen op die dag; Het zal Hem dienen met offers en gaven, Gelofte afleggen aan Jahweh, en trouw ze volbrengen. 22Zo zal Jahweh Egypte kastijden: Het slaan ter genezing! En wanneer ze zich dan tot Jahweh bekeren, Zal Hij zich laten verbidden, en hen weer genezen! 23Op die dag zal er een heirbaan ontstaan Van Egypte naar Assjoer; Assjoer zal naar Egypte komen, Egypte naar Assjoer, En Egypte zal samen met Assjoer hem dienen! 24En op die dag Zal Israël als derde Met Egypte en Assjoer een zegen ontvangen In het midden der aarde! 25Jahweh der heirscharen zal ze zegenen, En zeggen: Gezegend Egypte, mijn volk; Assjoer, het werk mijner handen; Israël, mijn erfdeel!