አሞጽ 7 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

አሞጽ 7:1-17

አንበጣ፣ እሳትና ቱንቢ

1ጌታ እግዚአብሔር ይህን አሳየኝ፤ የንጉሡ የመኸር እህል ከተሰበሰበ በኋላ ገቦው መብቀል በጀመረ ጊዜ፣ እርሱ የአንበጣ መንጋ እንዲፈለፈል አደረገ። 2አንበጦች የምድሩን ሣር ግጠው ከጨረሱት በኋላ፣ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ ይቅር እንድትል እለምንሃለሁ፤ ያዕቆብ ይህን እንዴት ሊቋቋመው ይችላል? ታናሽ ነው እኮ!” አልሁ።

3እግዚአብሔርም ስለዚህ ነገር ተጸጸተ፤ እግዚአብሔርም ይህ አይፈጸምም አለ።

4ጌታ እግዚአብሔር ይህንም አሳየኝ፤ ጌታ እግዚአብሔር በእሳት ሊፈርድ ተዘጋጀ፤ እሳቱም ታላቁን ጥልቅ አደረቀ፤ ምድሪቱንም በላ። 5ከዚያም በኋላ፣ “ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንድትተወው እለምንሃለሁ፤ ያዕቆብ ይህን እንዴት ሊቋቋመው ይችላል? ታናሽ ነው እኮ!” አልሁ።

6እግዚአብሔር ስለዚህ ነገር ተጸጸተ፤ ጌታ እግዚአብሔር፣ “ይህም ደግሞ አይፈጸምም” አለ።

7ይህንም ደግሞ አሳየኝ፤ ጌታ በእጁ ቱንቢ ይዞ በቱንቢ በተሠራ ቅጥር አጠገብ ቆሞ ነበር። 8እግዚአብሔር፣ “አሞጽ፣ የምታየው ምንድን ነው?” አለኝ።

እኔም፣ “ቱንቢ” አልሁ።

ጌታም እንዲህ አለ፤ “እነሆ፤ በሕዝቤ በእስራኤል መካከል ቱንቢ እዘረጋለሁ፤ ከእንግዲህም ወዲያ አልምራቸውም።

9“የይስሐቅ ማምለኪያ ኰረብታዎች ባድማ ይሆናሉ፤

የእስራኤል መቅደሶች ይፈርሳሉ፤

በኢዮርብዓምም ቤት ላይ በሰይፌ እነሣለሁ።”

አሞጽና አሜስያስ

10ከዚህ በኋላ የቤቴል ካህን አሜስያስ ወደ እስራኤል ንጉሥ ወደ ኢዮርብዓም እንዲህ ሲል መልእክት ላከ፤ “አሞጽ በእስራኤል ቤት መካከል በአንተ ላይ እያሤረ ነው፤ ምድሪቱም ቃሉን ሁሉ ልትሸከም አትችልም፤ 11አሞጽ እንዲህ ሲል ተናግሮ ነበርና፤

“ ‘ኢዮርብዓም በሰይፍ ይሞታል፤

እስራኤልም በርግጥ ከትውልድ አገሩ

ተማርኮ ይሄዳል።’ ”

12አሜስያስም፣ አሞጽን እንዲህ አለው፤ “አንተ ባለ ራእይ ከዚህ ሂድ! ከይሁዳ ምድር ሽሽ፤ እዚያም እንጀራህን ብላ፤ በዚያም ትንቢት ተናገር። 13ከእንግዲህ ወዲያ ግን በቤቴል ትንቢት አትናገር፤ የንጉሡ መቅደስ፣ የመንግሥቱም መኖሪያ ነውና።”

14አሞጽም ለአሜስያስ እንዲህ ሲል መለሰ፤ “እኔ እረኛና የባሉጥ ፍሬ ለቃሚ ነኝ እንጂ ነቢይ ወይም የነቢይ ልጅ አይደለሁም፤ 15እግዚአብሔር ግን የበግ መንጋ ከምጠብቅበት ቦታ ወስዶ፣ ‘ሂድና ለሕዝቤ ለእስራኤል ትንቢት ተናገር’ አለኝ፤ 16እንግዲህ የእግዚአብሔርን ቃል ስማ።

“አንተ፣ ‘በእስራኤል ላይ ትንቢት አትናገር፤

በይስሐቅም ቤት ላይ አትስበክ’

ትላለህ።

17“ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ ‘ሚስትህ በከተማዪቱ ውስጥ ጋለሞታ ትሆናለች፤

ወንዶችና ሴቶች ልጆችህም በሰይፍ ይወድቃሉ፤

ምድርህም እየተለካ ይከፋፈላል፤

አንተ ራስህ በረከሰ7፥17 ዕብራይስጡ ርኩስ ይለዋል። ምድር ትሞታለህ፤

እስራኤልም ከትውልድ አገሩ፣

ተማርኮ ይሄዳል።’ ”

Thai New Contemporary Bible

อาโมส 7:1-17

ตั๊กแตน ไฟ และสายดิ่ง

1พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตทรงสำแดงแก่ข้าพเจ้าดังนี้คือ พระองค์กำลังเตรียมฝูงตั๊กแตนจำนวนมหาศาลให้มาหลังจากเก็บเกี่ยวพืชผลส่วนของกษัตริย์แล้ว ขณะที่ผลผลิตรุ่นที่สองกำลังออกมา 2เมื่อตั๊กแตนเหล่านั้นกินพืชจนแผ่นดินโล่งเตียน ข้าพเจ้าก็ร้องทูลว่า “ข้าแต่พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตขอทรงอภัยเถิด! ยาโคบจะอยู่รอดได้อย่างไร? ในเมื่อเขาเล็กกระจ้อยร่อยเพียงนี้!”

3ดังนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าจึงทรงอดพระทัยไว้

องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “เหตุการณ์นี้จะไม่เกิดขึ้น”

4พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตทรงสำแดงแก่ข้าพเจ้าดังนี้คือ พระองค์ทรงเตรียมลงทัณฑ์ด้วยไฟ มันเผาผลาญห้วงสมุทรและไหม้แผ่นดิน 5แล้วข้าพเจ้าจึงร้องทูลว่า “ข้าแต่พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตขอทรงโปรดยับยั้งไว้เถิด! ยาโคบจะอยู่รอดได้อย่างไร? ในเมื่อเขาเล็กกระจ้อยร่อยเพียงนี้!”

6ดังนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าจึงทรงอดพระทัยไว้

พระยาห์เวห์องค์เจ้าชีวิตตรัสว่า “เหตุการณ์นี้ก็จะไม่เกิดขึ้นเช่นกัน”

7พระองค์ทรงสำแดงแก่ข้าพเจ้าดังนี้คือ องค์พระผู้เป็นเจ้าประทับยืนอยู่ข้างกำแพงที่สร้างขึ้นโดยใช้สายดิ่งวัด และมีสายดิ่งอยู่ในพระหัตถ์ 8และองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสถามข้าพเจ้าว่า “อาโมส เจ้าเห็นอะไร?”

ข้าพเจ้าทูลว่า “สายดิ่งพระเจ้าข้า”

แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “ดูเถิด เรากำลังจะวางสายดิ่งในหมู่ประชากรอิสราเอลของเรา เราจะไม่ละเว้นพวกเขาอีกต่อไป

9“บรรดาสถานบูชาบนที่สูงของอิสอัคจะถูกทำลายล้าง

และสถานนมัสการต่างๆ ของอิสราเอลจะถูกทำลาย

เราจะลุกขึ้นต่อสู้พงศ์พันธุ์ของเยโรโบอัมด้วยดาบของเรา”

อาโมสกับอามาซิยาห์

10แล้วอามาซิยาห์ปุโรหิตแห่งเบธเอลได้แจ้งข่าวต่อกษัตริย์เยโรโบอัมแห่งอิสราเอลว่า “อาโมสกำลังคบคิดวางแผนร้ายต่อพระองค์ที่ใจกลางอิสราเอลนี้เอง ถ้อยคำของเขาบ่อนทำลายชาติ 11เพราะอาโมสพูดว่า

“ ‘เยโรโบอัมจะตายด้วยดาบ

และอิสราเอลจะตกเป็นเชลยอย่างแน่นอน

ต้องไปจากบ้านเกิดเมืองนอน’ ”

12แล้วอามาซิยาห์กล่าวกับอาโมสว่า “ออกไปนะเจ้านักทำนาย! กลับไปแผ่นดินยูดาห์เสีย ไปทำมาหากินและเผยพระวจนะที่นั่น 13ไม่ต้องเผยพระวจนะที่เบธเอลนี้อีก เพราะที่นี่เป็นสถานนมัสการของกษัตริย์และเป็นวิหารของอาณาจักร”

14อาโมสตอบอามาซิยาห์ว่า “เมื่อก่อนข้าพเจ้าไม่ได้เป็นผู้เผยพระวจนะหรือเป็นลูกของผู้เผยพระวจนะ ข้าพเจ้าเป็นคนเลี้ยงแกะและดูแลสวนมะเดื่อ 15แต่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพาข้าพเจ้ามาจากงานเลี้ยงแกะ และตรัสสั่งข้าพเจ้าว่า ‘จงไปเผยพระวจนะแก่อิสราเอลประชากรของเรา’ 16บัดนี้จงฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้า เพราะท่านกล่าวว่า

“ ‘อย่าเผยพระวจนะแง่ร้ายต่ออิสราเอล

และหยุดเทศนาติเตียนพงศ์พันธุ์ของอิสอัค’

17“ฉะนั้นองค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า

“ ‘ภรรยาของเจ้าจะกลายเป็นโสเภณีกลางเมือง

และบุตรชายบุตรสาวของเจ้าจะตายด้วยคมดาบ

ที่ดินของเจ้าจะถูกวัดและถูกแบ่งแยก

ตัวเจ้าเองจะตายในดินแดนต่างศาสนา7:17 ภาษาฮีบรูว่าไปจากดินแดนที่เป็นมลทิน

และอิสราเอลจะตกเป็นเชลยอย่างแน่นอน

ต้องไปจากบ้านเกิดเมืองนอน’ ”