አሞጽ 1 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

አሞጽ 1:1-15

1በቴቁሔ ከነበሩት እረኞች መካከል አንዱ የሆነው አሞጽ፣ ዖዝያን የይሁዳ ንጉሥ በነበረ ጊዜ እንዲሁም የዮአስ1፥1 ዕብራይስጡ ዮአስ ያለው የኢዮአስ ተለዋጭ ስም ሳይሆን አይቀርም። ልጅ ኢዮርብዓም የእስራኤል ንጉሥ በነበረ ጊዜ፣ ይኸውም የምድር መናወጥ ከመሆኑ ከሁለት ዓመት በፊት ስለ እስራኤል ያየውና የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

2እርሱም እንዲህ አለ፤

እግዚአብሔር ከጽዮን ድምፁን ከፍ አድርጎ ያሰማል፤

ከኢየሩሳሌምም ያንጐደጕዳል፤

የእረኞች ማሰማሪያዎች ደርቀዋል1፥2 ወይም የእረኞች ሐዘን

የቀርሜሎስም ዐናት ጠውልጓል።”

በእስራኤል ጎረቤቶች ላይ የተሰጠ ፍርድ

3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የደማስቆ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

የብረት ጥርስ ባለው ማሄጃ፣

ገለዓድን አሂዳለችና፤

4የወልደ አዴርን ምሽጎች እንዲበላ፣

በአዛሄል ቤት ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

5የደማስቆን በሮች እሰባብራለሁ፤

በቤት ዔደን በትር የያዘውን፣

በአዌን1፥5 አዌን የቃሉ ትርጕም ክፋት እንደ ማለት ነው። ሸለቆ ያለውን ንጉሥ1፥5 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤

የሶርያም ሕዝብ ተማርኮ ወደ ቂር ይሄዳል”

ይላል እግዚአብሔር

6እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጋዛ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ በመውሰድ፣

ለኤዶም ሸጣለችና።

7ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጋዛ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

8በአስቀሎና በትር የያዘውን፣

የአሽዶድንም ንጉሥ1፥8 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤ በፍልስጥኤም ካሉት የመጨረሻው ሰው

እስኪሞት ድረስ፣

እጄን በአቃሮን ላይ እዘረጋለሁ፤”

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

9እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጢሮስ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም።

የወንድማማችነትን ቃል ኪዳን በማፍረስ፣

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ ለኤዶም ሸጣለችና።

10ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጢሮስ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

11እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የኤዶም ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ርኅራኄን1፥11 ወይም ሰይፍ ወይም ከእርሱ ጋር የተባበሩትን አጠፉ በመንፈግ፣

ወንድሙን በሰይፍ አሳድዶታልና፤

የቍጣውንም ነበልባል ሳይገድብ፣

መዓቱን ሳያቋርጥ አውርዶበታልና፤

12የባሶራን ምሽጎች እንዲበላ፣

በቴማን ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

13እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የአሞን ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ድንበሩን ለማስፋት፣

የገለዓድን ነፍሰ ጡር ሴቶች ሆድ ቀድዷልና።

14በጦርነት ቀን በጩኸት ውስጥ፣

በማዕበል ቀን በዐውሎ ነፋስ ውስጥ፣

ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በረባት ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

15ንጉሧ1፥15 ወይም ሞሎክ በዕብራይስጡ ማልካም ይላል። ከሹማምቱ ጋር፣

በአንድነት ተማርኮ ይሄዳል፣”

ይላል እግዚአብሔር

Ketab El Hayat

عاموس 1:1-15

1هَذِهِ كَلِمَاتُ عَامُوسَ الَّذِي كَانَ رَاعِياً مِنْ رُعَاةِ تَقُوعَ، يُنْبِئُ فِيهَا بِمَا رَآهُ بِشَأْنِ إِسْرَائِيلَ فِي أَيَّامِ عُزِّيَّا مَلِكِ يَهُوذَا، وَفِي أَيَّامِ يَرُبْعَامَ بْنِ يُوآشَ مَلِكِ إِسْرَائِيلَ، قَبْلَ وُقُوعِ الزَّلْزَلَةِ بِسَنَتَيْنِ.

2قَالَ: «يَزْأَرُ الرَّبُّ مِنْ صِهْيَوْنَ وَيُدَوِّي بِصَوْتِهِ مِنْ أُورُشَلِيمَ، فَتَنْتَحِبُ مَرَاعِي الرُّعَاةِ، وَتَذْوِي قِمَّةُ الْكَرْمَلِ.

قضاء الله على جيران إسرائيل

3هَذَا مَا يَقُولُهُ الرَّبُّ: مِنْ أَجْلِ مَعَاصِي دِمَشْقَ الثَّلاثِ وَالأَرْبَعِ لَنْ أَرُدَّ عَنْهَا سَخَطِي، لأَنَّ أَهْلَهَا قَدْ دَاسُوا شَعْبِي فِي جِلْعَادَ بِنَوَارِجَ مِنْ حَدِيدٍ. 4لِذَلِكَ أُرْسِلُ نَاراً عَلَى بَيْتِ حَزَائِيلَ فَتَلْتَهِمُ حُصُونَ بَنْهَدَدَ. 5وَأُحَطِّمُ مِزْلاجَ دِمَشْقَ وَأَسْتَأْصِلُ أَهْلَ وَادِي آوَنَ، وَأُهْلِكُ حَامِلَ صَوْلَجَانِ مُلْكِ بَيْتِ عَدْنٍ، وَيُسَاقُ شَعْبُ أَرَامَ إِلَى السَّبْيِ إِلَى أَرْضِ قِيرَ.

6هَذَا مَا يَقُولُهُ الرَّبُّ: مِنْ أَجْلِ مَعَاصِي غَزَّةَ الثَّلاثِ وَالأَرْبَعِ لَنْ أَرُدَّ عَنْهَا سَخَطِي، لأَنَّ أَهْلَهَا نَفَوْا شَعْباً عَنْ آخِرِهِ لِيُسَلِّمُوهُ إِلَى أَدُومَ. 7لِذَلِكَ سَأُرْسِلُ نَاراً عَلَى أَسْوَارِ غَزَّةَ تَلْتَهِمُ حُصُونَهَا. 8وَأَسْتَأْصِلُ أَهْلَ أَشْدُودَ، وَأُهْلِكُ حَامِلَ صَوْلَجَانِ مُلْكِ أَشْقَلُونَ، وَأُوَجِّهُ ضَرَبَاتِي ضِدَّ عَقْرُونَ فَيَفْنَى مَنْ بَقِيَ مِنَ الْفِلِسْطِينِيِّينَ.

نبوءة عن صور

9هَذَا مَا يَقُولُهُ الرَّبُّ: مِنْ أَجْلِ مَعَاصِي صُورَ الثَّلاثِ وَالأَرْبَعِ لَنْ أَرُدَّ عَنْهَا سَخَطِي، لأَنَّ أَهْلَهَا سَلَّمُوا شَعْباً بِكَامِلِهِ إِلَى أَدُومَ، وَنَقَضُوا عَهْدَ الإِخْوَةِ. 10لِهَذَا أُرْسِلُ نَاراً عَلَى أَسْوَارِ صُورَ فَتَلْتَهِمُ حُصُونَهَا.

11وَهَذَا مَا يَقُولُهُ الرَّبُّ: مِنْ أَجْلِ مَعَاصِي أَدُومَ الثَّلاثِ وَالأَرْبَعِ لَنْ أَرُدَّ عَنْهُمْ سَخَطِي، لأَنَّهُمْ تَعَقَّبُوا إِخْوَتَهُمْ بِالسَّيْفِ، وَتَغَاضَوْا عَنْ كُلِّ رَحْمَةٍ، وَجَعَلُوا غَضَبَهُمْ يَتَأَجَّجُ مُلْتَهِماً بِاسْتِمْرَارٍ، وَظَلُّوا حَاقِدِينَ عَلَى الدَّوَامِ. 12فَأُرْسِلُ نَاراً عَلَى تَيْمَانَ، فَتَلْتَهِمُ حُصُونَ بُصْرَةَ.

13هَذَا مَا يَقُولُهُ الرَّبُّ: مِنْ أَجْلِ مَعَاصِي الْعَمُّونِيِّينَ الثَّلاثِ وَالأَرْبَعِ لَنْ أَرُدَّ عَنْهُمْ سَخَطِي، لأَنَّهُمْ شَقُّوا بُطُونَ الْحَوَامِلِ فِي جِلْعَادَ لِيُوَسِّعُوا تُخُمَهُمْ. 14لِهَذَا أُضْرِمُ نَاراً فِي سُورِ رَبَّةَ فَتَلْتَهِمُ حُصُونَهَا فِي مُعْتَرَكِ جَلَبَةِ يَوْمِ الْحَرْبِ، وَفِي وَسَطِ عَاصِفَةٍ فِي يَوْمِ الزَّوْبَعَةِ. 15وَيُسَاقُ مَلِكُهُمْ إِلَى السَّبْيِ مَعَ سَائِرِ رُؤَسَائِهِ يَقُولُ الرَّبُّ.