አሞጽ 1 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

አሞጽ 1:1-15

1በቴቁሔ ከነበሩት እረኞች መካከል አንዱ የሆነው አሞጽ፣ ዖዝያን የይሁዳ ንጉሥ በነበረ ጊዜ እንዲሁም የዮአስ1፥1 ዕብራይስጡ ዮአስ ያለው የኢዮአስ ተለዋጭ ስም ሳይሆን አይቀርም። ልጅ ኢዮርብዓም የእስራኤል ንጉሥ በነበረ ጊዜ፣ ይኸውም የምድር መናወጥ ከመሆኑ ከሁለት ዓመት በፊት ስለ እስራኤል ያየውና የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

2እርሱም እንዲህ አለ፤

እግዚአብሔር ከጽዮን ድምፁን ከፍ አድርጎ ያሰማል፤

ከኢየሩሳሌምም ያንጐደጕዳል፤

የእረኞች ማሰማሪያዎች ደርቀዋል1፥2 ወይም የእረኞች ሐዘን

የቀርሜሎስም ዐናት ጠውልጓል።”

በእስራኤል ጎረቤቶች ላይ የተሰጠ ፍርድ

3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የደማስቆ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

የብረት ጥርስ ባለው ማሄጃ፣

ገለዓድን አሂዳለችና፤

4የወልደ አዴርን ምሽጎች እንዲበላ፣

በአዛሄል ቤት ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

5የደማስቆን በሮች እሰባብራለሁ፤

በቤት ዔደን በትር የያዘውን፣

በአዌን1፥5 አዌን የቃሉ ትርጕም ክፋት እንደ ማለት ነው። ሸለቆ ያለውን ንጉሥ1፥5 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤

የሶርያም ሕዝብ ተማርኮ ወደ ቂር ይሄዳል”

ይላል እግዚአብሔር

6እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጋዛ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ በመውሰድ፣

ለኤዶም ሸጣለችና።

7ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጋዛ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

8በአስቀሎና በትር የያዘውን፣

የአሽዶድንም ንጉሥ1፥8 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤ በፍልስጥኤም ካሉት የመጨረሻው ሰው

እስኪሞት ድረስ፣

እጄን በአቃሮን ላይ እዘረጋለሁ፤”

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

9እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጢሮስ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም።

የወንድማማችነትን ቃል ኪዳን በማፍረስ፣

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ ለኤዶም ሸጣለችና።

10ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጢሮስ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

11እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የኤዶም ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ርኅራኄን1፥11 ወይም ሰይፍ ወይም ከእርሱ ጋር የተባበሩትን አጠፉ በመንፈግ፣

ወንድሙን በሰይፍ አሳድዶታልና፤

የቍጣውንም ነበልባል ሳይገድብ፣

መዓቱን ሳያቋርጥ አውርዶበታልና፤

12የባሶራን ምሽጎች እንዲበላ፣

በቴማን ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

13እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የአሞን ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ድንበሩን ለማስፋት፣

የገለዓድን ነፍሰ ጡር ሴቶች ሆድ ቀድዷልና።

14በጦርነት ቀን በጩኸት ውስጥ፣

በማዕበል ቀን በዐውሎ ነፋስ ውስጥ፣

ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በረባት ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

15ንጉሧ1፥15 ወይም ሞሎክ በዕብራይስጡ ማልካም ይላል። ከሹማምቱ ጋር፣

በአንድነት ተማርኮ ይሄዳል፣”

ይላል እግዚአብሔር

Japanese Contemporary Bible

アモス書 1:1-15

1

1アモスはテコアの村に住む羊飼いでした。一日中、丘の中腹にいて、羊が迷い出ないように見張っていたのです。

イスラエルの隣人へのさばき

2ある日、神はアモスに、イスラエルに起ころうとしていることを幻の中で語りました。この幻をアモスが見たのは、ウジヤがユダの王、ヨアシュの子ヤロブアムがイスラエルの王であった時で、地震が起こる二年前のことでした。

アモスは見聞きしたことを、次のように報告しています。

主は、ねぐらからほえるどう猛なライオンのように、

シオンの山にある神殿から、大声で叫びました。

すると突然、カルメル山のみずみずしい牧草地が

しおれて枯れ、羊飼いはみな、声を上げて泣きました。

3主はこう言います。

「ダマスコの民は何度もくり返して罪を犯し、

わたしはそのことを忘れない。

もうこれ以上、処罰を猶予しない。

彼らは穀物を鉄の打穀棒で打つように、

ギルアデでわたしの民を打った。

4だから、ハザエル王の宮殿に火を放ち、

ベン・ハダデの堅固なとりでを破壊する。

5ダマスコの町の門のかんぬきを折り、

アベンの平野に住む者や、

ベテ・エデンで王位についている者を殺す。

シリヤの民は奴隷としてキルに戻る。」

6主はこう言います。

「ガザは何度もくり返して罪を犯し、

わたしはそのことを忘れない。

もうこれ以上、処罰を猶予しない。

ガザはわたしの民を追い出し、

エドムで奴隷として売った。

7だから、ガザの城壁に火を放ち、

とりではすべて破壊される。

8アシュドデの民を殺し、

エクロンと、アシュケロンの王を滅ぼそう。

残ったペリシテ人は滅びる。」

9主はこう言います。

「ツロの民は何度もくり返して罪を犯し、

わたしはそのことを忘れない。

もうこれ以上、処罰を猶予しない。

彼らは兄弟であるイスラエルとの協定を破り、

攻撃をしかけて征服し、奴隷としてエドムに渡した。

10だから、ツロの城壁に火を放ち、

とりでも宮殿も灰にする。」

11主はこう言います。

「エドムは何度もくり返して罪を犯し、

わたしはそのことを忘れない。

もうこれ以上、処罰を猶予しない。

彼らは兄弟であるイスラエルを剣で追いかけ、

怒りにまかせて冷酷にふるまった。

12だから、テマンに火をかけ、

ボツラのとりでをすべて灰にする。」

13主はこう言います。

「アモンの民は何度もくり返して罪を犯し、

わたしはそのことを忘れない。

もうこれ以上、処罰を猶予しない。

彼らはギルアデの戦いで、領土を広げるために

残虐なことを行い、剣で妊婦を切り裂いた。

14だから、ラバの城壁に火を放ち、

とりでと宮殿は灰となる。

嵐の時のつむじ風のように、

戦いのものすごい叫び声が上がる。

15王も君主たちも捕囚として連れ去られる。」