አሞጽ 1 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

አሞጽ 1:1-15

1በቴቁሔ ከነበሩት እረኞች መካከል አንዱ የሆነው አሞጽ፣ ዖዝያን የይሁዳ ንጉሥ በነበረ ጊዜ እንዲሁም የዮአስ1፥1 ዕብራይስጡ ዮአስ ያለው የኢዮአስ ተለዋጭ ስም ሳይሆን አይቀርም። ልጅ ኢዮርብዓም የእስራኤል ንጉሥ በነበረ ጊዜ፣ ይኸውም የምድር መናወጥ ከመሆኑ ከሁለት ዓመት በፊት ስለ እስራኤል ያየውና የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

2እርሱም እንዲህ አለ፤

እግዚአብሔር ከጽዮን ድምፁን ከፍ አድርጎ ያሰማል፤

ከኢየሩሳሌምም ያንጐደጕዳል፤

የእረኞች ማሰማሪያዎች ደርቀዋል1፥2 ወይም የእረኞች ሐዘን

የቀርሜሎስም ዐናት ጠውልጓል።”

በእስራኤል ጎረቤቶች ላይ የተሰጠ ፍርድ

3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የደማስቆ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

የብረት ጥርስ ባለው ማሄጃ፣

ገለዓድን አሂዳለችና፤

4የወልደ አዴርን ምሽጎች እንዲበላ፣

በአዛሄል ቤት ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

5የደማስቆን በሮች እሰባብራለሁ፤

በቤት ዔደን በትር የያዘውን፣

በአዌን1፥5 አዌን የቃሉ ትርጕም ክፋት እንደ ማለት ነው። ሸለቆ ያለውን ንጉሥ1፥5 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤

የሶርያም ሕዝብ ተማርኮ ወደ ቂር ይሄዳል”

ይላል እግዚአብሔር

6እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጋዛ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ በመውሰድ፣

ለኤዶም ሸጣለችና።

7ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጋዛ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

8በአስቀሎና በትር የያዘውን፣

የአሽዶድንም ንጉሥ1፥8 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤ በፍልስጥኤም ካሉት የመጨረሻው ሰው

እስኪሞት ድረስ፣

እጄን በአቃሮን ላይ እዘረጋለሁ፤”

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

9እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጢሮስ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም።

የወንድማማችነትን ቃል ኪዳን በማፍረስ፣

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ ለኤዶም ሸጣለችና።

10ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጢሮስ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

11እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የኤዶም ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ርኅራኄን1፥11 ወይም ሰይፍ ወይም ከእርሱ ጋር የተባበሩትን አጠፉ በመንፈግ፣

ወንድሙን በሰይፍ አሳድዶታልና፤

የቍጣውንም ነበልባል ሳይገድብ፣

መዓቱን ሳያቋርጥ አውርዶበታልና፤

12የባሶራን ምሽጎች እንዲበላ፣

በቴማን ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

13እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የአሞን ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ድንበሩን ለማስፋት፣

የገለዓድን ነፍሰ ጡር ሴቶች ሆድ ቀድዷልና።

14በጦርነት ቀን በጩኸት ውስጥ፣

በማዕበል ቀን በዐውሎ ነፋስ ውስጥ፣

ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በረባት ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

15ንጉሧ1፥15 ወይም ሞሎክ በዕብራይስጡ ማልካም ይላል። ከሹማምቱ ጋር፣

በአንድነት ተማርኮ ይሄዳል፣”

ይላል እግዚአብሔር

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

阿摩司書 1:1-15

1猶大烏西雅約阿施的兒子以色列耶羅波安執政期間,大地震前兩年,提哥亞的牧人阿摩司看到了關於以色列的異象。以下是阿摩司的話。

2他說:

「耶和華在錫安1·2 錫安」位於耶路撒冷北部,即大衛城,有時用來指耶路撒冷。怒吼,

在耶路撒冷呼喊。

牧人的草場枯乾,

迦密山頂枯黃。」

對亞蘭的審判

3耶和華說:

大馬士革人三番四次地犯罪,

我必不收回對他們的懲罰,

因為他們用打糧食的鐵器蹂躪基列

4所以我要降火在哈薛王家,

燒毀便·哈達王的城堡。

5我要折斷大馬士革城的門閂,

剷除亞文平原1·5 亞文平原」希伯來文是「邪惡谷」。亞文平原和伯·伊甸皆屬於亞蘭人。的居民和伯·伊甸的掌權者,

使亞蘭人被擄到吉珥1·5 吉珥的位置不詳,亞蘭人原來自吉珥。

這是耶和華說的。」

對非利士的審判

6耶和華說:

迦薩人三番四次地犯罪,

我必不收回對他們的懲罰,

因為他們把被擄之人全都帶走,

賣到以東做奴隸。

7所以,我要降火在迦薩的城牆上,

燒毀它的城堡。

8我要剷除亞實突的居民和亞實基倫的掌權者,

伸手攻擊以革倫

剩下的非利士人都要滅亡。

這是主耶和華說的。」

對泰爾的審判

9耶和華說:

泰爾人三番四次地犯罪,

我必不收回對他們的懲罰,

因為他們背棄弟兄之盟,

把被擄之人都賣到以東

10所以,我要降火在泰爾的城牆上,

燒毀它的城堡。」

對以東的審判

11耶和華說:

以東人三番四次地犯罪,

我必不收回對他們的懲罰,

因為他們拔刀追趕自己的弟兄,

沒有半點憐憫之心;

他們怒氣不息,永懷憤怒。

12所以,我要降火在提幔

燒毀波斯拉的城堡。」

對亞捫的審判

13耶和華說:

亞捫人三番四次地犯罪,

我必不收回對他們的懲罰,

因為他們為了擴張領土,

竟剖開基列孕婦的肚腹。

14所以,我要在戰爭的吶喊聲中,

在暴風雨吹襲的時候,

降火在拉巴的城牆上,

燒毀它的城堡。

15他們的君王和首領都要被擄。

這是耶和華說的。」