አሞጽ 1 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

አሞጽ 1:1-15

1በቴቁሔ ከነበሩት እረኞች መካከል አንዱ የሆነው አሞጽ፣ ዖዝያን የይሁዳ ንጉሥ በነበረ ጊዜ እንዲሁም የዮአስ1፥1 ዕብራይስጡ ዮአስ ያለው የኢዮአስ ተለዋጭ ስም ሳይሆን አይቀርም። ልጅ ኢዮርብዓም የእስራኤል ንጉሥ በነበረ ጊዜ፣ ይኸውም የምድር መናወጥ ከመሆኑ ከሁለት ዓመት በፊት ስለ እስራኤል ያየውና የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

2እርሱም እንዲህ አለ፤

እግዚአብሔር ከጽዮን ድምፁን ከፍ አድርጎ ያሰማል፤

ከኢየሩሳሌምም ያንጐደጕዳል፤

የእረኞች ማሰማሪያዎች ደርቀዋል1፥2 ወይም የእረኞች ሐዘን

የቀርሜሎስም ዐናት ጠውልጓል።”

በእስራኤል ጎረቤቶች ላይ የተሰጠ ፍርድ

3እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የደማስቆ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

የብረት ጥርስ ባለው ማሄጃ፣

ገለዓድን አሂዳለችና፤

4የወልደ አዴርን ምሽጎች እንዲበላ፣

በአዛሄል ቤት ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

5የደማስቆን በሮች እሰባብራለሁ፤

በቤት ዔደን በትር የያዘውን፣

በአዌን1፥5 አዌን የቃሉ ትርጕም ክፋት እንደ ማለት ነው። ሸለቆ ያለውን ንጉሥ1፥5 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤

የሶርያም ሕዝብ ተማርኮ ወደ ቂር ይሄዳል”

ይላል እግዚአብሔር

6እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጋዛ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ በመውሰድ፣

ለኤዶም ሸጣለችና።

7ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጋዛ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

8በአስቀሎና በትር የያዘውን፣

የአሽዶድንም ንጉሥ1፥8 ወይም ነዋሪዎች እደመስሳለሁ፤ በፍልስጥኤም ካሉት የመጨረሻው ሰው

እስኪሞት ድረስ፣

እጄን በአቃሮን ላይ እዘረጋለሁ፤”

ይላል ጌታ እግዚአብሔር

9እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የጢሮስ ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም።

የወንድማማችነትን ቃል ኪዳን በማፍረስ፣

ሕዝቡን ሁሉ ማርካ ለኤዶም ሸጣለችና።

10ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በጢሮስ ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

11እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የኤዶም ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ርኅራኄን1፥11 ወይም ሰይፍ ወይም ከእርሱ ጋር የተባበሩትን አጠፉ በመንፈግ፣

ወንድሙን በሰይፍ አሳድዶታልና፤

የቍጣውንም ነበልባል ሳይገድብ፣

መዓቱን ሳያቋርጥ አውርዶበታልና፤

12የባሶራን ምሽጎች እንዲበላ፣

በቴማን ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።”

13እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“ስለ ሦስቱ የአሞን ኀጢአት፣

ይልቁንም ስለ አራቱ፣ ቍጣዬን አልመልስም፤

ድንበሩን ለማስፋት፣

የገለዓድን ነፍሰ ጡር ሴቶች ሆድ ቀድዷልና።

14በጦርነት ቀን በጩኸት ውስጥ፣

በማዕበል ቀን በዐውሎ ነፋስ ውስጥ፣

ምሽጎቿን እንዲበላ፣

በረባት ቅጥሮች ላይ እሳት እሰድዳለሁ።

15ንጉሧ1፥15 ወይም ሞሎክ በዕብራይስጡ ማልካም ይላል። ከሹማምቱ ጋር፣

በአንድነት ተማርኮ ይሄዳል፣”

ይላል እግዚአብሔር

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

阿摩司书 1:1-15

1犹大乌西雅约阿施的儿子以色列耶罗波安执政期间,大地震前两年,提哥亚的牧人阿摩司看到了关于以色列的异象。以下是阿摩司的话。

2他说:

“耶和华在锡安1:2 锡安”位于耶路撒冷北部,即大卫城,有时用来指耶路撒冷。怒吼,

在耶路撒冷呼喊。

牧人的草场枯干,

迦密山顶枯黄。”

对亚兰的审判

3耶和华说:

大马士革人三番四次地犯罪,

我必不收回对他们的惩罚,

因为他们用打粮食的铁器蹂躏基列

4所以我要降火在哈薛王家,

烧毁便·哈达王的城堡。

5我要折断大马士革城的门闩,

铲除亚文平原1:5 亚文平原”希伯来文是“邪恶谷”。亚文平原和伯·伊甸皆属于亚兰人。的居民和伯·伊甸的掌权者,

使亚兰人被掳到吉珥1:5 吉珥的位置不详,亚兰人原来自吉珥。

这是耶和华说的。”

对非利士的审判

6耶和华说:

迦萨人三番四次地犯罪,

我必不收回对他们的惩罚,

因为他们把被掳之人全都带走,

卖到以东做奴隶。

7所以,我要降火在迦萨的城墙上,

烧毁它的城堡。

8我要铲除亚实突的居民和亚实基伦的掌权者,

伸手攻击以革伦

剩下的非利士人都要灭亡。

这是主耶和华说的。”

对泰尔的审判

9耶和华说:

泰尔人三番四次地犯罪,

我必不收回对他们的惩罚,

因为他们背弃弟兄之盟,

把被掳之人都卖到以东

10所以,我要降火在泰尔的城墙上,

烧毁它的城堡。”

对以东的审判

11耶和华说:

以东人三番四次地犯罪,

我必不收回对他们的惩罚,

因为他们拔刀追赶自己的弟兄,

没有半点怜悯之心;

他们怒气不息,永怀愤怒。

12所以,我要降火在提幔

烧毁波斯拉的城堡。”

对亚扪的审判

13耶和华说:

亚扪人三番四次地犯罪,

我必不收回对他们的惩罚,

因为他们为了扩张领土,

竟剖开基列孕妇的肚腹。

14所以,我要在战争的吶喊声中,

在暴风雨吹袭的时候,

降火在拉巴的城墙上,

烧毁它的城堡。

15他们的君王和首领都要被掳。

这是耶和华说的。”