ናሆም 3 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

ናሆም 3:1-19

ለነነዌ

1ለደም ከተማ ወዮላት!

ሐሰት፣ ዘረፋም ሞልቶባታል፤

ብዝበዛዋ ተግዞ አያልቅም።

2የጅራፍ ድምፅ፣

የመንኰራኵር ኳኳቴ፣

የፈጣን ፈረስ ኰቴ፣

የሠረገሎች ድምፅ ተሰምቷል።

3ፈረሰኛው ይጋልባል፤

ሰይፍ ይንቦገቦጋል፤

ጦር ያብረቀርቃል።

የሞተው ብዙ ነው፤

ሬሳ በሬሳ ሆኗል፤

ስፍር ቍጥር የለውም፤

መተላለፊያ አልተገኘም።

4ይህ ሁሉ የሆነው ቅጥ ባጣች፣

አሳሳችና መተተኛ በሆነች ዘማዊት ምክንያት ነው፤

እርሷም በዝሙቷ አሕዛብን፣

በጥንቈላዋም ሕዝቦችን ባሪያ ያደረገች ናት።

5የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እኔ በጠላትነት ተነሥቼብሻለሁ፤

ቀሚስሽን እስከ ፊትሽ እገልበዋለሁ፤

ዕርቃንሽን ለአሕዛብ፣

ኀፍረትሽንም ለነገሥታት አሳያለሁ።

6ቈሻሻ እደፋብሻለሁ፤

እንቅሻለሁ፤

ማላገጫም አደርግሻለሁ።

7የሚያዩሽ ሁሉ ከአንቺ እየሸሹ፣

‘ነነዌ ፈራርሳለች፤ ማን ያለቅስላታል?’ ይላሉ፤

የሚያጽናናሽንስ ከወዴት አገኛለሁ?”

8አንቺ በአባይ ወንዝ አጠገብ ካለችው፣

በውሃ ከተከበበችው፣

ከኖእ አሞን3፥8 አንዳንዶች ቴብስ ይላሉ። ትበልጫለሽን?

ወንዙ መከላከያዋ፣

ውሃውም ቅጥሯ ነው።

9ኢትዮጵያና ግብፅ ወሰን የለሽ ኀይሏ ናቸው፤

ፉጥና ሊቢያም ረዳቶቿ ነበሩ።

10ይሁን እንጂ በምርኮ ተወሰደች፤

ተሰድዳም ሄደች።

በየመንገዱ ማእዘን ላይ፣

ሕፃናቷ ተፈጠፈጡ፤

በመሳፍንቷ ላይ ዕጣ ተጣለ፤

ታላላቅ ሰዎቿ ሁሉ በሰንሰለት ታሰሩ።

11አንቺ ደግሞ ትሰክሪአለሽ፤

ትደበቂአለሽ፣

ከጠላትም መሸሸጊያ ትፈልጊአለሽ።

12ምሽጎችሽ ሁሉ ሊበሉ እንደ ደረሱ

የመጀመሪያ በለስ ፍሬ ናቸው፤

በሚወዛወዙበት ጊዜ፣

ፍሬዎቹ በበላተኛው አፍ ውስጥ ይወድቃሉ።

13እነሆ፤ ጭፍሮችሽ፣

ሁሉም ሴቶች ናቸው!

የምድርሽ በሮች፣

ለጠላቶችሽ ወለል ብለው ተከፍተዋል፤

መዝጊያዎቻቸውንም እሳት በልቷቸዋል።

14ለከበባው ውሃ ቅጅ፤

መከላከያሽን አጠናክሪ፤

የሸክላውን ዐፈር ፈልጊ፤

ጭቃውን ርገጪ፤

ጡቡንም ሥሪ።

15በዚያ እሳት ይበላሻል፤

ሰይፍ ይቈርጥሻል፤

እንደ ኵብኵባም ይግጥሻል።

እንደ ኵብኵባ እርቢ፤

እንደ አንበጣም ተባዢ።

16ከሰማይ ከዋክብት እስኪበልጡ ድረስ፣

የነጋዴዎችሽን ቍጥር አበዛሽ፤

ምድሪቱን ግን እንደ አንበጣ ግጠው አሟጠጡ፤

ከዚያም በርረው ሄዱ።

17ጠባቂዎችሽ እንደ አንበጣ፣

መኳንንትሽም በብርድ ቀን

በቅጥር ሥር እንደሚቀመጥ ኵብኵባ ናቸው፤

ፀሓይ ሲወጣ ግን ይበርራሉ፤

የት እንደሚበርሩም አይታወቅም።

18የአሦር ንጉሥ ሆይ፤ እረኞችህ3፥18 ገዦች ማለት ነው። አንቀላፉ፤

መኳንንትህ ዐርፈው ተኙ፤

ሕዝብህ ሰብሳቢ ዐጥተው፣

በተራራ ላይ ተበትነዋል።

19ቍስልህን ሊፈውስ የሚችል የለም፤

ስብራትህም ለሞት የሚያደርስ ነው።

ስለ አንተ የሰማ ሁሉ፣

በውድቀትህ ደስ ብሎት ያጨበጭባል፤

ወሰን የሌለው ጭካኔህ

ያልነካው ማን አለና?

Japanese Contemporary Bible

ナホム書 3:1-19

3

ニネベの災い

1ああ、流血の町、

偽りと略奪に満ちたニネベは災いだ。

2聞け、むちの音を。

戦車がニネベに向かって進んで来る。

車輪とひづめの音を響かせて、

荒々しく通りを走り抜けて行く。

その音のすさまじいことよ。

3騎兵が振りかざす剣と槍が、きらめいているのを見よ。

死人が通りに横たわっている。

どこもかしこも死体の山だ。

人々はそれにつまずいて転び、ようやく置き上がり、

再び倒れる。

4こうなったのもみな、

ニネベが神の敵に自分を売ったからだ。

美しいが不誠実な町、死に至らせる魅力をもつ女王は、

その美しさで国々の気を引き、

彼らすべてに偽りの神々を拝むことを教えて、

あらゆる場所で人々を魅了した。

5全能の主は言う。

「わたしがおまえに反対するのは当然のことだ。

今、全地がおまえの裸と恥を見ることになる。

6おまえを汚物で覆い、

実際どんなに汚い者であるかを世界に見せよう。」

7おまえを見る者はみな、恐れてしりごみする。

「ニネベは完全に廃墟と化した」と。

それでも、おまえの運命を悲しむ者は一人もいない。

8おまえは、ナイル川の両岸にまたがり、

四方を川で守られていたテーベよりも

すぐれているだろうか。

9エチオピヤとエジプト全土はテーベの力強い同盟者で、

テーベはプテとリビヤからと同様、

彼らからどんな援助でも求めることができた。

10それでもテーベは陥落し、

住民は奴隷となって連れて行かれたのだ。

赤ん坊は道路の石にたたきつけられて死んだ。

高官たちは、くじ引きで兵士たちの召使にされた。

指導者はみな鎖につながれた。

11ニネベも、酔っぱらいのようにふらつき、

おびえて身を隠すようになる。

12要塞はすべて陥落する。

木を揺さぶる人の口の中に落ちる、

初なりのいちじくのように食べられる。

13おまえの軍隊は女のように弱く、頼る相手がいない。

国のすべての門は敵に対して広く開けられ、

火で焼かれる。

14籠城に備えよ。水をたくわえよ。要塞を強固にせよ。

城壁を修理するために、れんがをたくさん用意せよ。

洞窟に入って粘土を足でこね、型に詰めるのだ。

15しかし、準備の最中に、火がおまえを焼き尽くす。

剣がおまえを切り倒す。

若いいなごが目の前にある物を平らげるように、

敵がおまえを食い尽くす。

おまえはばったのように増え広がるが、

逃れることはできない。

16商人は星のように多く、

巨万の富でこの町を満たしたが、

敵はいなごのように群がり、それを持ち去る。

17君主や役人たちは、いなごが寒い季節に

生け垣に群がるように、群がっている。

ところが、日が昇って地が暖まりだすと

いなごも姿を消すように、全員が逃げていなくなる。

18アッシリヤの王よ。

おまえの君主たちは、死んでちりの中に横たわる。

おまえの民は山の向こうに散らされる。

今、彼らを集める牧者はいない。

19おまえの傷は治らない。

あまりにも傷が深いからだ。

おまえの最期を聞く者はみな、手をたたいて喜ぶ。

みな、おまえの残虐なふるまいに苦しんだからだ。