ቲቶ 3 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ቲቶ 3:1-15

በጎ የሆነውን ማድረግ

1ሰዎች ለገዦችና ለባለሥልጣናት እንዲገዙ፣ እንዲታዘዙና መልካም የሆነውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ እንዲሆኑ አሳስባቸው። 2እንዲሁም በማንም ላይ ክፉ እንዳይናገሩ፣ ሰላማውያን እንዲሆኑ፣ ለሰዎችም ሁሉ ከልብ የመነጨ ትሕትና እንዲያሳዩ አስገንዝባቸው።

3ቀደም ሲል እኛ ራሳችን ማስተዋል የጐደለን፣ የማንታዘዝ፣ የተታለልን፣ ለተለያየ ምኞትና ምቾት ባሪያ ሆነን የተገዛን ነበርን፤ እየተጣላንና እርስ በርስ እየተጠላላን በክፋትና በምቀኝነት እንኖር ነበር። 4ነገር ግን የአዳኛችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ፍቅር በተገለጠ ጊዜ፣ 5ስላደረግነው የጽድቅ ሥራ ሳይሆን፣ ከምሕረቱ የተነሣ አዳነን። ያዳነንም ዳግም ልደት በሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ መታደስ ነው፤ 6ይህንም መንፈስ እግዚአብሔር በአዳኛችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእኛ ላይ አትረፍርፎ አፈሰሰው፤ 7ይኸውም በጸጋው ጸድቀን የዘላለምን ሕይወት ተስፋ ይዘን ወራሾች እንድንሆን ነው። 8ይህም የታመነ ቃል ነው። በእግዚአብሔር ያመኑቱ መልካሙን ነገር ለማድረግ ራሳቸውን አሳልፈው ይሰጡ ዘንድ እነዚህን ነገሮች አስረግጠህ እንድትናገር እፈልጋለሁ። ይህ መልካምና ለማንኛውም ሰው የሚጠቅም ነው።

9ነገር ግን ከንቱ ከሆነ ክርክርና ከትውልድ ሐረግ ቈጠራ፣ ከጭቅጭቅና ስለ ሕግ ከሚነሣ ጠብ ራቅ፤ ይህ ዋጋ ቢስና ከንቱ ነውና። 10መከፋፈል የሚያመጣን ሰው አንድ ጊዜ ምከረው፤ ለሁለተኛ ጊዜ አስጠንቅቀው፤ ከዚያ ካለፈ ከእርሱ ጋር አንዳች ነገር አይኑርህ። 11እንዲህ ዐይነቱ ሰው የሳተና ኀጢአተኛ ነው፤ ራሱንም እንደሚኰንን ዕወቅ።

የመጨረሻ ምክር

12አርጢሞንን ወይም ቲኪቆስን ወደ አንተ እንደ ላክሁ እኔ ወዳለሁበት ወደ ኒቆጵልዮን ለመምጣት የተቻለህን ሁሉ አድርግ፤ ክረምቱን በዚያ ላሳልፍ ወስኛለሁ። 13ሕግ ዐዋቂውን ዜማስንና አጵሎስን በጕዟቸው ለመርዳት የተቻለህን ሁሉ አድርግ፤ የሚያስፈልጋቸውንም ሁሉ አሟላላቸው።

14ከእኛ ወገን የሆኑት ለዕለት የሚያስፈልጋቸውን እንዲያገኙና ኑሯቸውም ፍሬ የሌለው እንዳይሆን ለመልካም ሥራ መትጋትን ይማሩ ዘንድ ይገባቸዋል።

15ከእኔ ጋር ያሉት ሁሉ ሰላምታ ያቀርቡላችኋል።

ከእምነት የተነሣ ለሚወድዱን ሰላምታ አቅርቡልን።

ጸጋ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።

New International Reader’s Version

Titus 3:1-15

Do What Is Good Because You Are Saved

1Remind God’s people to obey rulers and authorities. Remind them to be ready to do what is good. 2Tell them not to speak evil things against anyone. Remind them to live in peace. They must consider the needs of others. They must always be gentle toward everyone.

3At one time we too acted like fools. We didn’t obey God. We were tricked. We were controlled by all kinds of desires and pleasures. We were full of evil. We wanted what belongs to others. People hated us, and we hated one another. 4But the kindness and love of God our Savior appeared. 5He saved us. It wasn’t because of the good things we had done. It was because of his mercy. He saved us by washing away our sins. We were born again. The Holy Spirit gave us new life. 6God poured out the Spirit on us freely. That’s because of what Jesus Christ our Savior has done. 7His grace made us right with God. So now we have received the hope of eternal life as God’s children. 8You can trust this saying. These things are important. Treat them that way. Then those who trust in God will be careful to commit themselves to doing good. These things are excellent. They are for the good of everyone.

9But keep away from foolish disagreements. Don’t argue about family histories. Don’t make trouble. Don’t fight about what the law teaches. Don’t argue about things like that. It doesn’t do any good. It doesn’t help anyone. 10Warn anyone who tries to get believers to separate from one another. Warn that person more than once. After that, have nothing to do with them. 11You can be sure that people like this are twisted and sinful. Their own actions judge them.

Final Words

12I will send Artemas or Tychicus to you. Then do your best to come to me at Nicopolis. I’ve decided to spend the winter there. 13Do everything you can to help Zenas the lawyer and Apollos. Send them on their way. See that they have everything they need.

14Our people must learn to commit themselves to doing what is good. Then they can provide for people when they are in great need. If they do that, their lives won’t turn out to be useless.

15Everyone who is with me sends you greetings.

Greet those who love us in the faith.

May God’s grace be with you all.