ራእይ 8 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ራእይ 8:1-13

ሰባተኛው ማኅተምና የወርቁ ጥና

1በጉ ሰባተኛውን ማኅተም በፈታ ጊዜ፣ ግማሽ ሰዓት ያህል በሰማይ ዝምታ ሆነ።

2ከዚያም በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ፤ ሰባት መለከትም ተሰጣቸው።

3ሌላም መልአክ የወርቅ ጥና ይዞ መጣና በመሠዊያው አጠገብ ቆመ፤ እርሱም በዙፋኑ ፊት ባለው የወርቅ መሠዊያ ላይ ከቅዱሳን ጸሎት ሁሉ ጋር እንዲያቀርበው ብዙ ዕጣን ተሰጠው። 4የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳኑ ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ ወደ እግዚአብሔር ፊት ወጣ። 5መልአኩም ጥናውን ይዞ የመሠዊያውን እሳት ሞላበትና ወደ ምድር ወረወረው፤ ነጐድጓድ፣ ድምፅ፣ መብረቅና የምድር መናወጥ ሆነ።

ሰባቱ መለከቶች

6ከዚያም ሰባቱን መለከት የያዙት ሰባቱ መላእክት ለመንፋት ተዘጋጁ።

7የመጀመሪያው መልአክ መለከቱን ነፋ፤ ደም የተቀላቀለበት በረዶና እሳት ወደ ምድር ተጣለ፤ የምድር አንድ ሦስተኛ ተቃጠለ፤ የዛፎችም አንድ ሦስተኛ ተቃጠለ፤ የለመለመውም ሣር ሁሉ ተቃጠለ።

8ሁለተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤ ትልቅ ተራራ የሚመስል ነገር በእሳት እየተቀጣጠለ ወደ ባሕር ተጣለ፤ የባሕሩ አንድ ሦስተኛ ወደ ደም ተለወጠ፤ 9በባሕሩም ውስጥ ከሚኖሩት ሕያዋን ፍጡራን አንድ ሦስተኛ ሞተ፤ የመርከቦችም አንድ ሦስተኛ ወደመ።

10ሦስተኛውም መልአክ መለከቱን ነፋ፤ እንደ ችቦ የሚነድድ ታላቅ ኮከብ በወንዞች አንድ ሦስተኛና በውሃ ምንጮች ላይ ከሰማይ ወደቀ፤ 11የኮከቡም ስም “እሬቶ8፥11 ምሬት ማለት ነው።” ይባል ነበር። የውሃውም አንድ ሦስተኛ መራራ ሆነ፤ ውሃው መራራ ከመሆኑ የተነሣም ብዙ ሰዎች ሞቱ።

12አራተኛው መልአክ መለከቱን ነፋ፤ የብርሃናቸው አንድ ሦስተኛ ይጨልም ዘንድ፣ የፀሓይ አንድ ሦስተኛ፣ የጨረቃም አንድ ሦስተኛ፣ የከዋክብትም አንድ ሦስተኛ ተመታ፤ የቀንም አንድ ሦስተኛ፣ የሌሊቱም አንድ ሦስተኛ ብርሃን እንዳይሰጥ ተከለከለ።

13ከዚያም ተመለከትሁ፤ አንድ ንስር በሰማይ መካከል ይበርር ነበር፤ በታላቅ ድምፅም፣ “የቀሩት ሦስቱ መላእክት መለከት ስለሚነፉ፣ በምድር ላይ ለሚኖሩት ወዮላቸው! ወዮላቸው! ወዮላቸው!” ሲል ሰማሁ።

Knijga O Kristu

Otkrivenje 8:1-13

Jaganjac razlama sedmi pečat

1Kad je Jaganjac razlomio sedmi pečat, u nebu nastane muk otprilike pola ure. 2Ugledam zatim kako su sedam anđela koji stoje pred Bogom dobili sedam trubalja.

3Još jedan anđeo, sa zlatnom kadionicom, stane pred žrtvenik. Dobio je mnogo kada da ga s molitvama Božjega naroda prinese na zlatni žrtvenik pred prijestoljem. 4Kadni dim pomiješan s molitvama svetih vine se s oltara, kamo ih je anđeo izlio, pred Boga. 5Anđeo zatim napuni kadionicu vatrom sa žrtvenika i prospe ju na zemlju. Razlegnu se gromovi i grmljavina, bljesnu munje i nastane potres.

Prve četiri trublje

6Sedam anđela sa sedam trublja priprave se da zatrube.

7Prvi zatrubi. Na zemlju se prospu tuča i oganj pomiješani s krvlju. Izgori trećina zemlje, trećina stabala i sva zelena trava.

8Zatrubi i drugi anđeo. Nešto poput velike ognjene gore padne u more. Trećina se voda u moru pretvori u krv. 9Trećina svih živih stvorenja u moru ugine i trećina lađa propadne.

10Zatrubi treći anđeo. Golema ognjena zvijezda padne s neba poput goruće zublje. Padne na trećinu rijeka i izvora. 11Zvijezda se zove Pelin. Od nje se trećina voda pretvori u pelin te mnoštvo ljudi umre od gorke vode.

12Zatrubi četvrti anđeo. Trećina sunca, trećina mjeseca i trećina zvijezda udareni su tako da se pomrače za trećinu. I dan i noć izgube trećinu svojega sjaja.

13Pogledam gore i začujem orla kako leteći zrakom glasno viče: “Teško, teško, teško stanovnicima zemlje kad zatrube posljednja trojica anđela!”