ራእይ 19 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ራእይ 19:1-21

ሃሌ ሉያ

1ከዚህ በኋላ የብዙ ሰዎችን ድምፅ የሚመስል ታላቅ ድምፅ በሰማይ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

“ሃሌ ሉያ!

ማዳን፣ ክብርና ኀይል የአምላካችን ነው፤

2ፍርዱ እውነትና ጽድቅ ነውና፤

በዝሙቷ ምድርን ያረከሰችውን፣

ታላቂቱን አመንዝራ ፈርዶባታል፤

ስለ አገልጋዮቹም ደም ተበቅሏታል።”

3ደግሞም እንዲህ አሉ፤

“ሃሌ ሉያ!

ጢስ ከእርሷ ከዘላለም እስከ ዘላለም ይወጣል።”

4ሃያ አራቱ ሽማግሌዎችና አራቱ ሕያዋን ፍጡራን በዙፋኑ ላይ ለተቀመጠው አምላክ ወድቀው ሰገዱ፤ እንዲህም አሉ፤

“አሜን፣ ሃሌ ሉያ!”

5ከዚህ በኋላ እንዲህ የሚል ድምፅ ከዙፋኑ ወጣ፤

“እናንተ አገልጋዮቹ ሁሉ፣

እርሱን የምትፈሩ፣

ታናናሾችና ታላላቆችም፣

አምላካችንን አመስግኑ!”

6ደግሞም እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ፣ እንደ ኀይለኛ ወራጅ ውሃ ድምፅ፣ እንደ ብርቱም ነጐድጓድ ድምፅ የሚመስል እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

“ሃሌ ሉያ!

ሁሉን ቻይ ጌታ አምላካችን ነግሧልና።

7የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ፣

የእርሱም ሙሽራ ራሷን ስላዘጋጀች

ደስ ይበለን፤ ሐሤት እናድርግ፤

ክብርም እንስጠው።

8የሚያንጸባርቅና ንጹሕ፣

ከተልባ እግር የተሠራ ቀጭን ልብስ እንድትለብስ ተሰጣት።”

ከተልባ እግር የተሠራው ቀጭን ልብስ የቅዱሳን የጽድቅ ሥራ ነው።

9መልአኩም፣ “ ‘ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁዓን ናቸው’ ብለህ ጻፍ” አለኝ፤ ቀጥሎም፣ “እነዚህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ቃሎች ናቸው” አለኝ።

10እኔም ልሰግድለት በእግሩ ሥር ተደፋሁ፤ እርሱ ግን፣ “ተው! ይህን አታድርግ! እኔም ከአንተና የኢየሱስን ምስክር ከያዙት ወንድሞችህ ጋር አገልጋይ ነኝ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ፤ የኢየሱስ ምስክር የትንቢት መንፈስ ነውና” አለኝ።

በነጭ ፈረስ ላይ የተቀመጠው

11ከዚያም ሰማይም ተከፍቶ አየሁ፤ እነሆ አንድ ነጭ ፈረስ ነበረ፤ በፈረሱም ላይ፣ “ታማኝና እውነተኛ” የሚባል ተቀምጦ ነበር፤ እርሱም በጽድቅ ይፈርዳል፤ ይዋጋልም። 12ዐይኖቹ እንደ እሳት ነበልባል ናቸው፤ በራሱም ላይ ብዙ ዘውዶች አሉ። ከእርሱ በቀር ማንም የማያውቀው ስም በእርሱ ላይ ተጽፏል። 13እርሱ በደም የተነከረ ልብስ ለብሷል፤ ስሙም የእግዚአብሔር ቃል ነው። 14የሰማይም ሰራዊት ነጭ፣ ንጹሕና ከተልባ እግር የተሠራ ቀጭን ልብስ ለብሰው፣ በነጫጭ ፈረሶች ላይ ተቀምጠው ይከተሉት ነበር። 15ሕዝቦችን የሚመታበት ስለታም ሰይፍ ከአፉ ወጣ፤ “በብረት በትርም ይገዛቸዋል።” እርሱም ሁሉን ቻይ የሆነውን የእግዚአብሔርን የብርቱ ቍጣ ወይን መጭመቂያ ይረግጣል። 16በልብሱና በጭኑ ላይ እንዲህ የሚል ስም ተጽፏል፤

“የነገሥታት ንጉሥና የጌቶች ጌታ።”

17ቀጥሎም አንድ መልአክ በፀሓይ ውስጥ ቆሞ አየሁ፤ እርሱም በሰማይ መካከል ለሚበርሩ ወፎች ሁሉ እንዲህ ሲል በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ “ኑ፤ ወደ ታላቁ የእግዚአብሔር እራት ተሰብሰቡ፤ 18የምትሰበሰቡትም የነገሥታትን ሥጋ፣ የጦር አዛዦችን ሥጋ፣ የብርቱ ሰዎችን ሥጋ፣ የፈረሶችንና የፈረሰኞችን ሥጋ እንዲሁም የሰዎችን ሁሉ፣ ይኸውም የጌቶችንና የባሮችን፣ የታናናሾችንና የታላላቆችን ሥጋ እንድትበሉ ነው።”

19ከዚህ በኋላ አውሬው፣ የምድር ነገሥታትና ሰራዊታቸው በፈረሱ ላይ ከተቀመጠውና ከሰራዊቱ ጋር ለመዋጋት ተሰብስበው አየሁ። 20ነገር ግን አውሬው ተያዘ፤ ከእርሱም ጋር በፊቱ ምልክቶችን ያደርግ የነበረው ሐሰተኛው ነቢይ ተያዘ። በእነዚህ ምልክቶች የአውሬውን ምልክት የተቀበሉትንና ለምስሉ የሰገዱትን አሳተ። ሁለቱም በሕይወት እንዳሉ በዲን ወደሚቃጠለው የእሳት ባሕር ተጣሉ። 21የቀሩት ደግሞ በፈረሱ ላይ ከተቀመጠው አፍ በሚወጣው ሰይፍ ተገደሉ፤ ወፎችም ሁሉ ከሥጋቸው በልተው ጠገቡ።

New International Version

Revelation 19:1-21

Threefold Hallelujah Over Babylon’s Fall

1After this I heard what sounded like the roar of a great multitude in heaven shouting:

“Hallelujah!

Salvation and glory and power belong to our God,

2for true and just are his judgments.

He has condemned the great prostitute

who corrupted the earth by her adulteries.

He has avenged on her the blood of his servants.”

3And again they shouted:

“Hallelujah!

The smoke from her goes up for ever and ever.”

4The twenty-four elders and the four living creatures fell down and worshiped God, who was seated on the throne. And they cried:

“Amen, Hallelujah!”

5Then a voice came from the throne, saying:

“Praise our God,

all you his servants,

you who fear him,

both great and small!”

6Then I heard what sounded like a great multitude, like the roar of rushing waters and like loud peals of thunder, shouting:

“Hallelujah!

For our Lord God Almighty reigns.

7Let us rejoice and be glad

and give him glory!

For the wedding of the Lamb has come,

and his bride has made herself ready.

8Fine linen, bright and clean,

was given her to wear.”

(Fine linen stands for the righteous acts of God’s holy people.)

9Then the angel said to me, “Write this: Blessed are those who are invited to the wedding supper of the Lamb!” And he added, “These are the true words of God.”

10At this I fell at his feet to worship him. But he said to me, “Don’t do that! I am a fellow servant with you and with your brothers and sisters who hold to the testimony of Jesus. Worship God! For it is the Spirit of prophecy who bears testimony to Jesus.”

The Heavenly Warrior Defeats the Beast

11I saw heaven standing open and there before me was a white horse, whose rider is called Faithful and True. With justice he judges and wages war. 12His eyes are like blazing fire, and on his head are many crowns. He has a name written on him that no one knows but he himself. 13He is dressed in a robe dipped in blood, and his name is the Word of God. 14The armies of heaven were following him, riding on white horses and dressed in fine linen, white and clean. 15Coming out of his mouth is a sharp sword with which to strike down the nations. “He will rule them with an iron scepter.”19:15 Psalm 2:9 He treads the winepress of the fury of the wrath of God Almighty. 16On his robe and on his thigh he has this name written:

king of kings and lord of lords.

17And I saw an angel standing in the sun, who cried in a loud voice to all the birds flying in midair, “Come, gather together for the great supper of God, 18so that you may eat the flesh of kings, generals, and the mighty, of horses and their riders, and the flesh of all people, free and slave, great and small.”

19Then I saw the beast and the kings of the earth and their armies gathered together to wage war against the rider on the horse and his army. 20But the beast was captured, and with it the false prophet who had performed the signs on its behalf. With these signs he had deluded those who had received the mark of the beast and worshiped its image. The two of them were thrown alive into the fiery lake of burning sulfur. 21The rest were killed with the sword coming out of the mouth of the rider on the horse, and all the birds gorged themselves on their flesh.