ራእይ 15 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ራእይ 15:1-8

ሰባቱ መላእክትና ሰባቱ መቅሠፍቶች

1ሌላም ታላቅና አስደናቂ ምልክት በሰማይ አየሁ፤ የመጨረሻዎቹን ሰባት መቅሠፍቶች የያዙ ሰባት መላእክት አየሁ፤ የመጨረሻ የተባሉትም የእግዚአብሔር ቍጣ የሚፈጸመው በእነርሱ በመሆኑ ነው። 2ከእሳት ጋር የተቀላቀለ የብርጭቆ ባሕር የሚመስል አየሁ፤ በባሕሩም አጠገብ አውሬውን፣ ምስሉንና የስሙን ቍጥር ድል የነሡትን ቆመው አየሁ፤ እነርሱም ከእግዚአብሔር የተሰጣቸውን በገና ይዘው፣ 3የእግዚአብሔር ባሪያ የሆነውን የሙሴን መዝሙርና የበጉን መዝሙር እንዲህ እያሉ ይዘምሩ ነበር፤

“ሁሉን ቻይ ጌታ አምላክ ሆይ፤

ሥራህ ታላቅና አስደናቂ ነው።

የዘመናት15፥3 አንዳንድ የጥንት ቅጆች ሕዝቦች ይላሉ። ንጉሥ ሆይ፤

መንገድህ ጽድቅና እውነት ነው።

4ጌታ ሆይ፤ አንተን የማይፈራ፣

ስምህን የማያከብርስ ማን ነው?

አንተ ብቻ ቅዱስ ነህና።

የጽድቅ ሥራህ ስለ ተገለጠ፣

ሕዝቦች ሁሉ ይመጣሉ፤

በፊትህም ይሰግዳሉ።”

5ከዚህ በኋላም አየሁ፤ በሰማይ ያለው ቤተ መቅደስ፣ ይኸውም የምስክሩ ድንኳን ተከፍቶ ነበር። 6ሰባቱን መቅሠፍቶች የያዙት ሰባቱ መላእክት ከቤተ መቅደሱ ወጡ፤ እነርሱም ከተልባ እግር የተሠራ ንጹሕ የሚያበራ ልብስ ለብሰው፣ ደረታቸውንም በወርቅ መታጠቂያ ታጥቀው ነበር። 7ከዚያም ከአራቱ ሕያዋን ፍጡራን አንዱ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሚኖረው አምላክ ቍጣ የተሞሉትን ሰባት የወርቅ ጽዋዎች ለሰባቱ መላእክት ሰጣቸው። 8ቤተ መቅደሱም ከእግዚአብሔር ክብር፣ ከኀይሉም በወጣው ጢስ ተሞላ፤ የሰባቱ መላእክት ሰባት መቅሠፍቶች እስኪፈጸሙ ድረስ ማንም ወደ ቤተ መቅደሱ መግባት አልቻለም።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

התגלות 15:1-8

1אחר כך ראיתי בשמים חזיון מסתורי נוסף: שבעה מלאכים נושאים שבע מגפות. אלה הן המכות האחרונות, כי יחד איתן בא הקץ לזעמו של אלוהים.

2ראיתי מולי מעין ים זכוכית ואש, ועליו עומדים כל אלה שהתגברו על החיה הרעה, על פסלה, על סימן החותם שלה ועל מספרה. כולם החזיקו בידיהם את כינורות האלוהים, 3‏-4ושרו את שירת משה עבד אלוהים ואת שירת השה:

”גדולים ונפלאים מעשיך,

ה׳ אלוהי צבאות.

צדק ואמת דרכיך,

ה׳ מלך הגויים.

מי לא ירא מפניך, ה׳?

ומי לא ייתן כבוד לשמך?

כי אתה לבדך קדוש.

כל העמים יבואו וישתחוו לפניך,

כי נגלו מעשיך הצודקים.“

5אחרי כן ראיתי את קודש הקודשים בהיכל השמים נפתח לרווחה, 6ומתוכו יצאו שבעת המלאכים שנשאו את שבע המכות. הם לבשו גלימות לבנות, צחורות וטהורות, ועל החזה חגרו חגורות זהב. 7אחת מארבע החיות הגישה לכל אחד מהשבעה קערת זהב מלאה בזעם האלוהים החי לנצח.

8ההיכל נמלא עשן מגבורתו של אלוהים ומכבודו, ואיש לא יכול היה להיכנס לתוכו עד שסיימו שבעת המלאכים להכות את הארץ בשבע המגפות.