ራእይ 10 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

ራእይ 10:1-11

መልአኩና ትንሿ መጽሐፍ

1ከዚህ በኋላ ሌላ ብርቱ መልአክ ደመና ተጐናጽፎ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ እርሱም በራሱ ላይ ቀስተ ደመና ነበር። ፊቱ እንደ ፀሓይ፣ እግሮቹ እንደ እሳት ዐምዶች ነበሩ። 2በእጁም የተከፈተች ትንሽ ጥቅልል መጽሐፍ ይዞ ነበር፤ ቀኝ እግሩን በባሕር ላይ፣ ግራ እግሩን በምድር ላይ አኖረ፤ 3እንደሚያገሣ አንበሳም ድምፁን ከፍ አድርጎ ጮኸ፤ በጮኸም ጊዜ የሰባቱ ነጐድጓዶች ድምፆች ተናገሩ። 4ሰባቱ ነጐድጓዶች በተናገሩ ጊዜ፣ ለመጻፍ ተዘጋጀሁ፤ ነገር ግን፣ “ሰባቱ ነጐድጓዶች የተናገሩትን በማኅተም ዝጋው እንጂ አትጻፍ” የሚል ድምፅ ከሰማይ ሰማሁ።

5ከዚህ በኋላ በባሕርና በምድር ላይ ቆሞ ያየሁት መልአክ ቀኝ እጁን ወደ ሰማይ አነሣ፤ 6እርሱም ከዘላለም እስከ ዘላለም በሚኖረው፣ ሰማይንና በውስጡ ያሉትን፣ ምድርንና በውስጧ ያሉትን፣ ባሕርንና በውስጡ ያሉትን በፈጠረው በእርሱ ማለ፤ እንዲህም አለ፤ “ከእንግዲህ መዘግየት አይኖርም፤ 7ነገር ግን ሰባተኛው መልአክ መለከቱን በሚነፋባቸው ቀኖች፣ ለአገልጋዮቹ ለነቢያት በገለጠላቸው መሠረት የእግዚአብሔር ምስጢር ይፈጸማል።”

8ከዚያም ከሰማይ የሰማሁት ድምፅ እንደ ገና እንዲህ ሲል ተናገረ፤ “ሂድ፤ በባሕርና በምድር ላይ ከቆመው መልአክ እጅ የተከፈተችውን ጥቅልል መጽሐፍ ውሰድ።”

9እኔም ወደ መልአኩ ሄጄ ትንሿን ጥቅልል መጽሐፍ እንዲሰጠኝ ጠየቅሁት፤ እርሱም፣ “ውሰድና ብላት፤ ሆድህን መራራ ታደርገዋለች፤ በአፍህ ግን እንደ ማር ትጣፍጣለች” አለኝ። 10ትንሿንም መጽሐፍ ከመልአኩ እጅ ተቀብዬ በላኋት፤ በአፌ እንደ ማር ጣፈጠች፤ ከበላኋት በኋላ ግን ሆዴ መራራ ሆነ፤ 11ከዚያም፣ “ስለ ብዙ ሕዝቦች፣ ወገኖች፣ ቋንቋዎችና ነገሥታት እንደ ገና ትንቢት ልትናገር ይገባሃል” ተባልሁ።

New International Reader’s Version

Revelation 10:1-11

The Angel and the Little Scroll

1Then I saw another mighty angel coming down from heaven. He was wearing a cloud like a robe. There was a rainbow above his head. His face was like the sun. His legs were like pillars of fire. 2He was holding a little scroll. It was lying open in his hand. The angel put his right foot on the sea and his left foot on the land. 3Then he gave a loud shout like the roar of a lion. When he shouted, the voices of the seven thunders spoke. 4When they had spoken, I was getting ready to write. But I heard a voice from heaven say, “Seal up what the seven thunders have said. Do not write it down.”

5I had seen an angel standing on the sea and on the land. This angel raised his right hand to heaven. 6He made a promise in the name of the God who lives for ever and ever. This is the God who created the sky, earth and sea and all that is in them. The angel said, “There will be no more waiting! 7God’s plan will be carried out. This will happen when the seventh angel is ready to blow his trumpet. God told all this to the prophets who served him long ago.”

8Then the voice I had heard from heaven spoke to me again. It said, “The angel is standing on the sea and on the land. Go and take the scroll from him. It is lying open in his hand.”

9So I went to the angel and asked him to give me the little scroll. He said to me, “Take it and eat it. It will become sour in your stomach. But ‘in your mouth it will taste as sweet as honey.’ ” (Ezekiel 3:3) 10I took the little scroll from the angel’s hand and ate it. In my mouth it tasted as sweet as honey. But when I had eaten it, it became sour in my stomach. 11Then I was told, “You must prophesy again about many peoples, nations, languages and kings.”