ምሳሌ 7 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 7:1-27

ከአመንዝራ ሴት መራቅ

1ልጄ ሆይ፤ ቃሌን ጠብቅ፤

ትእዛዜንም በውስጥህ አኑር።

2ትእዛዜን ጠብቅ፤ በሕይወት ትኖራለህ፤

ትምህርቴንም እንደ ዐይንህ ብሌን ተንከባከበው።

3በጣትህ ላይ እሰረው፤

በልብህ ጽላት ላይ ጻፈው።

4ጥበብን፣ “እኅቴ ነሽ” በላት፤

ማስተዋልንም፣ “ዘመዴ ነህ” በለው፤

5ከአመንዝራ ሴት፣

በአንደበቷም ከምታታልል ዘልዛላ ሴት ይጠብቁሃል።

6በቤቴ መስኮት፣

በዐይነ ርግቡ ወደ ውጭ ተመለከትሁ።

7ማስተዋል የጐደለውን ወጣት፣

ብስለት ከሌላቸው መካከል አየሁት፤

ከጕልማሶችም መካከል ለየሁት።

8የቤቷን አቅጣጫ ይዞ፣

በቤቷ ማእዘን አጠገብ ባለው መንገድ ያልፍ ነበር፤

9ቀኑ መሸትሸት ሲል፣

በውድቅት ሌሊት፣ በጽኑ ጨለማ።

10ከዚያም አንዲት ሴት ልታገኘው ወጣች፤

እንደ ዝሙት ዐዳሪ ለብሳ፣ ለማሳሳት ታጥቃ።

11ጯኺና ማን አለብኝ ባይ ናት፤

እግሮቿ ዐርፈው ቤት አይቀመጡም፤

12አንዴ በመንገድ፣ አንዴ በአደባባይ፣

በየማእዘኑም ታደባለች።

13አፈፍ አድርጋ ይዛ ሳመችው፤

ኀፍረቷንም ጥላ እንዲህ አለችው፤

14“በቤቴ የኅብረት መሥዋዕት7፥14 በተለምዶ የሰላም መሥዋዕት ይባላል። ማቅረብ ነበረብኝ፤

ዛሬ ስእለቴን ፈጸምሁ፤

15ስለዚህ አንተን ለማግኘት ወጣሁ፤

ፈልጌህ ነበር፤ ይኸው አገኘሁህ።

16ዐልጋዬን ከግብፅ የመጣ፣

ጌጠኛ በፍታ አልብሼዋለሁ።

17ዐልጋዬን፣

የከርቤ፣ የዓልሙንና የቀረፋ ሽቱ አርከፍክፌበታለሁ።

18ና፤ እስኪነጋ በጥልቅ ፍቅር እንርካ፤

በፍቅር ራሳችንን እናስደስት።

19ባሌ እቤት የለም፤

ሩቅ አገር ሄዷል።

20በገንዘብ የተሞላ ቦርሳ ወስዷል፤

ጨረቃዋ ሙሉ እስክትሆን አይመለስም።”

21በሚያግባቡ ቃላት አሳተችው፤

በለሰለሰ አንደበቷ አታለለችው።

22ለዕርድ እንደሚነዳ በሬ፣

ወደ ወጥመድ7፥22 የሱርሰት (የሰብዓ ሊቃናትም) ትርጕም እና ዕብራይስጡ ተላላ ይላሉ። እንደሚገባ አጋዘን፣7፥22 የዚህ ስንኝ የዕብራይስጡ ትርጓሜ በርግጠኝነት አይታወቅም።

ሳያንገራግር ተከተላት፤

23ፍላጻ ጕበቱን እስኪወጋው ድረስ፣

ሕይወቱን እንደሚያሳጣው ሳያውቅ፣

በርራ ወደ ወጥመድ እንደምትገባ ወፍ ሆነ።

24ልጆቼ ሆይ፤ አሁንም አድምጡኝ፤

የምለውንም ልብ ብላችሁ ስሙኝ።

25ልባችሁን ወደ መንገዷ አታዘንብሉ፤

ወደ ስሕተት ጐዳናዋም አትግቡ።

26አዋርዳ የጣለቻቸው ብዙ ናቸው፤

የገደለቻቸውም ስፍር ቍጥር የላቸውም።

27ቤቷ ወደ ሲኦል7፥27 ወይም መቃብር የሚወስድ፣

ወደ ሞት ማደሪያም የሚያወርድ ጐዳና ነው።

Ketab El Hayat

الأمثال 7:1-27

تحذير من إغواء الزانية

1يَا ابْنِي احْفَظْ أَقْوَالِي وَاذْخَرْ وَصَايَايَ مَعَكَ. 2أَطِعْ وَصَايَايَ فَتَحْيَا، وَصُنْ شَرِيعَتِي كَحَدَقَةِ عَيْنِكَ. 3اعْصِبْهَا عَلَى أَصَابِعِكَ، وَاكْتُبْهَا عَلَى صَفْحَاتِ قَلْبِكَ. 4قُلْ لِلْحِكْمَةِ: أَنْتِ أُخْتِي، وَلِلْفِطْنَةِ: أَنْتِ قَرِيبَتِي. 5فَهُمَا تَحْفَظَانِكَ مِنَ الْمَرْأَةِ الْعَاهِرَةِ، وَالزَّوْجَةِ الْفَاسِقَةِ الَّتِي تَتَمَلَّقُ بِكَلامِهَا.

6فَإِنِّي أَشْرَفْتُ مِنْ كُوَّةِ بَيْتِي، وَأَطْلَلْتُ مِنْ خِلالِ نَافِذَتِي، 7فَشَاهَدْتُ بَيْنَ الْبَنِينَ الْحَمْقَى شَابّاً مُجَرَّداً مِنَ الْفَهْمِ، 8يَجْتَازُ الطَّرِيقَ صَوْبَ الْمُنْعَطَفِ، بِاتِّجَاهِ الشَّارِعِ الْمُفْضِي إِلَى بَيْتِهَا. 9عِنْدَ الْغَسَقِ فِي الْمَسَاءِ تَحْتَ جُنْحِ اللَّيْلِ وَالظُّلْمَةِ. 10فَإِذَا بِامْرَأَةٍ تَسْتَقْبِلُهُ فِي زِيِّ زَانِيَةٍ وَقَلْبٍ مُخَادِعٍ. 11صَخَّابَةٌ وَجَامِحَةٌ لَا تَسْتَقِرُّ قَدَمَاهَا فِي بَيْتِهَا. 12تَرَاهَا تَارَةً فِي الْخَارِجِ، وَطَوْراً فِي سَاحَاتِ الأَسْوَاقِ، تَكْمُنُ عِنْدَ كُلِّ مُنْعَطَفٍ. 13فَأَمْسَكَتْهُ وَقَبَّلَتْهُ وَقَالَتْ لَهُ بِوَجْهٍ وَقِحٍ: 14«كَانَ عَلَيَّ أَنْ أُقَدِّمَ ذَبَائِحَ سَلامٍ، فَأَوْفَيْتُ الْيَوْمَ نُذُورِي. 15وَقَدْ خَرَجْتُ لاِسْتِقْبَالِكَ، بَعْدَ أَنْ بَحَثْتُ بِشَوْقٍ عَنْكَ حَتَّى وَجَدْتُكَ. 16قَدْ فَرَشْتُ سَرِيرِي بِأَغْطِيَةٍ كَتَّانِيَّةٍ مُوَشَّاةٍ مِنْ مِصْرَ، 17وَعَطَّرْتُ فِرَاشِي بِطِيبِ الْمُرِّ وَالْقِرْفَةِ. 18فَتَعَالَ لِنَرْتَوِيَ مِنَ الْحُبِّ حَتَّى الصَّبَاحِ، وَنَتَلَذَّذَ بِمُتَعِ الْغَرَامِ. 19فَإِنَّ زَوْجِي لَيْسَ فِي الْبَيْتِ، قَدْ مَضَى فِي رِحْلَةٍ بَعِيدَةٍ. 20وَأَخَذَ مَعَهُ صُرَّةً مُكْتَنِزَةً بِالْمَالِ، وَلَنْ يَعُودَ إِلّا عِنْدَ اكْتِمَالِ الْبَدْرِ». 21فَأَغْوَتْهُ بِكَثْرَةِ أَفَانِينِ كَلامِهَا، وَرَنَّحَتْهُ بِتَمَلُّقِ شَفَتَيْهَا. 22فَمَضَى عَلَى التَّوِّ فِي إِثْرِهَا، كَثَوْرٍ مَسُوقٍ إِلَى الذَّبْحِ، أَوْ أَيِّلٍ وَقَعَ فِي فَخٍّ. 23إِلَى أَنْ يَنْفُذَ سَهْمٌ فِي كَبِدِهِ، وَيَكُونَ كَعُصْفُورٍ مُنْدَفِعٍ إِلَى شَرَكٍ، لَا يَدْرِي أَنَّهُ قَدْ نُصِبَ لِلْقَضَاءِ عَلَيْهِ.

24وَالآنَ أَصْغُوا إِلَيَّ أَيُّهَا الأَبْنَاءُ، وَأَرْهِفُوا آذَانَكُمْ إِلَى أَقْوَالِ فَمِي: 25لَا تَجْنَحْ قُلُوبُكُمْ نَحْوَ طُرُقِهَا، وَلا تُحَوِّمْ فِي دُرُوبِهَا. 26فَمَا أَكْثَرَ الَّذِينَ طَرَحَتْهُمْ مُثْخَنِينَ بِالْجِرَاحِ، وَجَمِيعُ صَرْعَاهَا أَقْوِيَاءُ. 27إِنَّ بَيْتَهَا هُوَ طَرِيقُ الْهَاوِيَةِ الْمُؤَدِّي إِلَى مَخَادِعِ الْمَوْتِ.