ምሳሌ 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 4:1-27

ጥበብ ከሁሉ በላይ መሆኗ

1ልጆቼ ሆይ፤ የአባትን ምክር አድምጡ፤

ልብ ብላችሁ ስሙ፤ ማስተዋልንም ገንዘብ አድርጉ።

2በጎ ትምህርት እሰጣችኋለሁ፤

ስለዚህ ትምህርቴን አትተዉ።

3በአባቴ ቤት ገና ለግላጋ ወጣት፣

ለእናቴም አንድ ልጇ ብቻ በነበርሁ ጊዜ፣

4አባቴ እንዲህ ሲል አስተማረኝ፤

“ቃሌን በሙሉ በልብህ ያዝ፤

ትእዛዜንም ጠብቅ፤ በሕይወት ትኖራለህ።

5ጥበብን አግኛት፤ ማስተዋልን ያዛት፤

ቃሌን አትርሳ፤ ከእርሷም ዘወር አትበል።

6ጥበብን አትተዋት፤ እርሷም ከለላ ትሆንሃለች፤

አፍቅራት፤ እርሷም ትጠብቅሃለች።

7ጥበብ ታላቅ ነገር ናት፤ ስለዚህ ጥበብን አግኛት፤

ያለህን ሁሉ4፥7 ወይም ያገኘኸውን ሁሉ ብታስከፍልህም ማስተዋልን ገንዘብህ አድርጋት።

8ክብርን ስጣት፤ ከፍ ከፍ ታደርግሃለች፤

ዕቀፋት፤ ታከብርሃለች፤

9በራስህ ላይ ሞገሳማ አክሊል ትደፋልሃለች፤”

የክብር ዘውድም ታበረክትልሃለች።

10ልጄ ሆይ፤ አድምጠኝ፤ ቃሌንም ልብ በል፤

የሕይወት ዘመንህም ትበዛለች።

11በጥበብ ጐዳና አስተምርሃለሁ፤

ቀጥተኛውንም መንገድ አሳይሃለሁ።

12ስትሄድ ርምጃህ አይሰናከልም፤

ስትሮጥም አትደናቀፍም።

13ምክርን አጥብቀህ ያዛት፤ አትልቀቃት፤

ጠብቃት፤ ሕይወትህ ናትና።

14ወደ ኀጥኣን ጐዳና እግርህን አታንሣ፤

በክፉ ሰዎች መንገድ አትሂድ፤

15ከዚያ አትድረስ፤ አትጓዝበት፤

ሽሸው፤ መንገድህን ይዘህ ሂድ፤

16ክፉ ካላደረጉ አይተኙምና፤

ሰውን ካላሰናከሉ እንቅልፍ በዐይናቸው አይዞርም።

17የክፋት እንጀራ ይበላሉ፤

የዐመፅ ወይን ጠጅ ይጠጣሉ።

18የጻድቃን መንገድ ሙሉ ቀን እስኪሆን ድረስ፣

ብርሃኑ እየጐላ እንደሚሄድ የማለዳ ውጋጋን ነው።

19የክፉዎች መንገድ ግን እንደ ድቅድቅ ጨለማ ነው፤

ምን እንደሚያሰናክላቸውም አያውቁም።

20ልጄ ሆይ፤ የምነግርህን አስተውል፤

ቃሌንም በጥንቃቄ አድምጥ።

21ከእይታህ አታርቀው፤

በልብህም ጠብቀው፤

22ለሚያገኘው ሕይወት፤

ለመላው የሰው አካልም ጤንነት ነውና።

23ከሁሉም በላይ ልብህን ጠብቅ፤

የሕይወት ምንጭ ነውና።

24ጥመትን ከአፍህ አስወግድ፤

ብልሹ ንግግርም ከከንፈሮችህ ይራቅ።

25ዐይኖችህ በቀጥታ ይመልከቱ፤

ትክ ብለህም ፊት ለፊት እይ።

26የእግርህን ጐዳና አስተካክል፤4፥26 ወይም ተመልከት

የጸናውን መንገድ ብቻ ያዝ።

27ወደ ቀኝ ወደ ግራ አትበል፤

እግርህን ከክፉ ጠብቅ።

Thai New Contemporary Bible

สุภาษิต 4:1-27

สละทุกอย่างเพื่อปัญญา

1ลูกทั้งหลายเอ๋ย จงตั้งใจฟังคำสั่งสอนของพ่อเจ้า

จงใส่ใจเพื่อจะได้ความเข้าใจ

2เพราะเราให้คำสอนที่ดีแก่เจ้า

ดังนั้นอย่าละทิ้งคำสอนของเรา

3เมื่อเราเป็นเด็กอยู่ในบ้านของพ่อ

ยังอ่อนเยาว์เป็นลูกรักของแม่

4พ่อสอนเราว่า

“จงยึดคำสอนของพ่อด้วยสุดใจของเจ้า

ทำตามคำสั่งของพ่อ แล้วเจ้าจะมีชีวิตอยู่

5จงรับปัญญาและความเข้าใจ

อย่าลืม อย่าหันเหจากคำสอนของพ่อ

6อย่าทอดทิ้งปัญญา แล้วนางจะช่วยปกปักรักษาเจ้า

จงรักนางแล้วนางจะคอยปกป้องเจ้า

7จุดเริ่มต้นของปัญญาคือให้ยึดปัญญาไว้

แม้ต้องลงทุนหมดตัวก็จงยึดความเข้าใจไว้

8จงเทิดทูนนาง และนางจะเชิดชูเจ้า

จงโอบกอดปัญญาไว้ และนางจะให้เกียรติเจ้า

9นางจะสวมมงคลงามบนศีรษะของเจ้า

มงกุฎงดงามจะเป็นของเจ้า”

10ลูกเอ๋ย จงฟังและรับถ้อยคำของเรา

เพื่อเจ้าจะมีชีวิตยืนยาว

11เราชี้แนะเจ้าไปในทางแห่งสติปัญญา

และนำเจ้าไปในทางตรง

12ยามเจ้าเดิน ย่างก้าวของเจ้าจะไม่ถูกขวางกั้น

ยามเจ้าวิ่ง เจ้าจะไม่สะดุด

13จงยึดคำสอนไว้ให้มั่น อย่าให้หลุดมือไป

จงรักษาไว้ให้ดี เพราะมันเป็นชีวิตของเจ้า

14อย่าย่างกรายเข้าไปในทางของคนชั่ว

หรือเดินในทางของคนเลว

15จงหลีกห่าง อย่าเดินไปบนทางนั้น

จงหันหนีและเลี่ยงไปทางอื่น

16เพราะสำหรับคนชั่วนั้น วันไหนไม่ได้ทำชั่วเขานอนไม่หลับ

เขาจะหลับตาไม่ลงจนกว่าจะได้ทำให้ใครล้มลงเสียก่อน

17เขาบริโภคความชั่วเป็นอาหาร

และดื่มเหล้าองุ่นแห่งความโหดเหี้ยมทารุณ

18ทางของคนชอบธรรมเป็นดั่งดวงอาทิตย์ยามรุ่งอรุณ

ซึ่งส่องแสงเจิดจ้าขึ้นเรื่อยๆ จนเต็มวัน

19แต่ทางของคนชั่วดั่งความมืดมิด

เขาไม่รู้ว่าตัวเองสะดุดอะไร

20ลูกเอ๋ย จงตั้งใจฟังสิ่งที่เรากล่าว

เงี่ยหูฟังถ้อยคำของเรา

21อย่าให้มันคลาดสายตาของเจ้า

จงรักษามันไว้ในใจของเจ้า

22เพราะมันเป็นชีวิตแก่ผู้ที่ค้นพบ

เป็นพลานามัยแก่ร่างกายทั้งหมดของเขา

23ที่สำคัญที่สุด จงระแวดระวังใจของเจ้า

เพราะทุกสิ่งที่เจ้าทำล้วนไหลออกมาจากใจ

24ให้ปากของเจ้าปราศจากคำตลบตะแลง

ให้ริมฝีปากของเจ้าห่างไกลจากคำหลอกลวง

25จงให้ตาของเจ้ามองตรงไปข้างหน้า

จดจ่อแน่วแน่ไม่หันเห

26จงเฝ้าระวังทุกย่างก้าวของเจ้า4:26 หรือจงทำทางที่ราบเรียบให้เท้าของเจ้า

และเดินอยู่ในทางนั้นอย่างมั่นคง

27อย่าหันไปทางขวาหรือทางซ้าย

จงยั้งเท้าของเจ้าไว้จากความชั่วร้าย