ምሳሌ 29 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 29:1-27

1ከብዙ ተግሣጽ በኋላ ዐንገቱን የሚያደነድን ሰው፣

በድንገት ይጠፋል፤ መዳኛም የለውም።

2ጻድቃን ሥልጣን ሲይዙ ሕዝብ ሐሤት ያደርጋል፤

ክፉዎች ሲገዙ ግን ሕዝብ ያቃስታል።

3ጥበብን የሚወድድ ሰው አባቱን ደስ ያሰኛል፤

የአመንዝራዎች ወዳጅ ግን ሀብቱን ያባክናል።

4ፍትሕን በማስፈን ንጉሥ አገርን ያረጋጋል፤

ጕቦ ለማግኘት የሚጐመጅ ግን ያፈራርሳታል።

5ባልንጀራውን የሚሸነግል፣

ለገዛ እግሩ መረብ ይዘረጋል።

6ክፉ ሰው በራሱ ኀጢአት ይጠመዳል፤

ጻድቅ ግን ይዘምራል፤ ደስም ይለዋል።

7ጻድቅ ለድኾች ፍትሕ ይጨነቃል፤

ክፉ ሰው ግን ደንታ የለውም።

8ተሳዳቢዎች ከተማን ያውካሉ፤

ጠቢባን ግን ቍጣን ያበርዳሉ።

9ጠቢብ ሰው ከተላላ ጋር ወደ ሸንጎ ቢሄድ፣

ተላላ ይቈጣል፤ ያፌዛል፤ ሰላምም አይኖርም።

10ደም የተጠሙ ሰዎች ሐቀኛን ሰው ይጠላሉ፤

ቅን የሆነውንም ለመግደል ይሻሉ።

11ተላላ ሰው ቍጣውን ያለ ገደብ ይለቅቀዋል፤

ጠቢብ ሰው ግን ራሱን ይቈጣጠራል።

12ገዥ የሐሰት ወሬ የሚሰማ ከሆነ፣

ሹማምቱ ሁሉ ክፉዎች ይሆናሉ።

13ድኻውና ጨቋኙ የጋራ ነገር አላቸው፤

እግዚአብሔር ለሁለቱም የዐይን ብርሃንን ሰጥቷቸዋል።

14ንጉሥ ለድኻ ትክክለኛ ፍርድ ቢሰጥ፣

ዙፋኑ ዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

15የተግሣጽ በትር ጥበብን ታጐናጽፋለች፤

መረን የተለቀቀ ልጅ ግን እናቱን ያሳፍራል።

16ክፉዎች ሥልጣን ሲይዙ ኀጢአት ይበዛል፤

ጻድቃን ግን የእነርሱን ውድቀት ያያሉ።

17ልጅህን ቅጣው፤ ሰላም ይሰጥሃል፤

ነፍስህንም ደስ ያሰኛታል።

18ራእይ በሌለበት ሕዝብ መረን ይሆናል፤

ሕግን የሚጠብቅ ግን የተባረከ ነው።

19አገልጋይ በቃል ብቻ ሊታረም አይችልም፤

ቢያስተውለውም እንኳ በጀ አይልም።

20በችኰላ የሚናገርን ሰው ታያለህን?

ከእርሱ ይልቅ ተላላ ተስፋ አለው።

21ሰው አገልጋዩን ከልጅነቱ ጀምሮ ቢያቀማጥል፣

የኋላ ኋላ ሐዘን29፥21 በዕብራይስጡ የዚህ ቃል ትርጓሜ በርግጠኝነት አይታወቅም። ያገኘዋል።

22ቍጡ ሰው ጠብን ይጭራል፤

ግልፍተኛም ብዙ ኀጢአት ይሠራል።

23ሰውን ትዕቢቱ ያዋርደዋል፤

ትሑት መንፈስ ያለው ግን ክብርን ይጐናጸፋል።

24የሌባ ግብረ አበር የገዛ ራሱ ጠላት ነው፤

የመሐላውን ርግማን እየሰማ ጭጭ ይላል።

25ሰውን መፍራት ወጥመድ ነው፤

በእግዚአብሔር የሚታመን ግን በሰላም ይኖራል።

26ብዙዎች በገዥ ፊት ተደማጭነት ማግኘት ይሻሉ፤

ሰው ፍትሕ የሚያገኘው ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

27ጻድቃን አታላዮችን ይጸየፋሉ፤

ክፉዎችም ቅኖችን ይጠላሉ።

Ketab El Hayat

الأمثال 29:1-27

1مَنْ كَثُرَ تَوْبِيخُهُ وَظَلَّ مُعْتَصِماً بِعِنَادِهِ، يَتَحَطَّمُ فَجْأَةً وَلا شِفَاءَ لَهُ. 2إِذَا سَادَ الأَبْرَارُ فَرِحَ الشَّعْبُ، وَإذَا تَسَلَّطَ الأَشْرَارُ أَنَّ النَّاسُ. 3مُحِبُّ الْحِكْمَةِ يُفَرِّحُ أَبَاهُ، وَعَشِيرُ الزَّوَانِي يُتْلِفُ مَالَهُ. 4بِالْعَدْلِ يُشِيعُ الْمَلِكُ الاسْتِقْرَارَ فِي أَرْضِهِ، وَالْمُوْلَعُ بِالرِّشْوَةِ يُدَمِّرُهَا. 5الْمَرْءُ الَّذِي يَتَمَلَّقُ صَاحِبَهُ يَنْشُرُ شَبَكَةً لِرِجْلَيْهِ. 6الشِّرِّيرُ مُقْتَنَصٌ فِي شَرَكِ إِثْمِهِ، أَمَّا الصِّدِّيقُ فَيَشْدُو وَيَبْتَهِجُ. 7الصِّدِّيقُ يُدْرِكُ حَقَّ الْفَقِيرِ، أَمَّا الشِّرِّيرُ فَلا يَعْبَأُ بِمَعْرِفَتِهِ. 8الْمُسْتَهْزِئُونَ يَفْتِنُونَ الْمَدِينَةَ، أَمَّا الْحُكَمَاءُ فَيَصْرِفُونَ الْغَضَبَ. 9إِنْ خَاصَمَ الْحَكِيمُ سَفِيهاً، فَلَنْ يَجِدَ رَاحَةً، سَوَاءٌ غَضِبَ السَّفِيهُ أَوْ ضَحِكَ. 10الْمُتَعَطِّشُونَ إِلَى الدِّمَاءِ يَكْرَهُونَ الْكَامِلَ، وَالأَشْرَارُ يَلْتَمِسُونَ هَلاكَ الْمُسْتَقِيمِ. 11الْجَاهِلُ يُفَجِّرُ غَضَبَهُ، أَمَّا الْحَكِيمُ فَيَكْبَحُهُ بِهُدُوءٍ.

12إِنْ أَصْغَى الْحَاكِمُ إِلَى الأَكَاذِيبِ، يَكُونُ جَمِيعُ رِجَالِ حَاشِيَتِهِ أَشْرَاراً لأَنَّهُمْ يَتَمَلَّقُونَهُ. 13فِي هَذَا يَتَشَابَهُ الْفَقِيرُ وَالظَّالِمُ، إِنَّ الرَّبَّ يُعْطِي نُوراً لِعَيْنَيْ كُلٍّ مِنْهُمَا. 14عَرْشُ الْمَلِكِ الْقَاضِي بِالْحَقِّ لِلْفُقَرَاءِ يَثْبُتُ إِلَى الأَبَدِ.

15الْعَصَا وَالتَّأْنِيبُ يُثْمِرَانِ حِكْمَةً، لَكِنَّ الصَّبِيَّ الْمُهْمَلَ يُخْجِلُ أُمَّهُ. 16إِذَا سَادَ الأَشْرَارُ كَثُرَتِ الآثَامُ، أَمَّا الأَبْرَارُ فَيَشْهَدُونَ سُقُوطَهُمْ. 17قَوِّمِ ابْنَكَ فَيُرِيحَكَ، وَيُشِيعَ الْمَسَرَّةَ فِي نَفْسِكَ. 18حَيْثُ لَا رُؤْيَا يَجْمَحُ الشَّعْبُ، وَطُوبَى لِمَنْ يَحْفَظُ الشَّرِيعَةَ. 19لَا تُؤَدِّبِ الْعَبْدَ بِمُجَرَّدِ الْكَلامِ، لأَنَّهُ وَإِنْ فَهِمَ لَا يَسْتَجِيبُ. 20أَرَأَيْتَ إِنْسَاناً مُتَهَوِّراً فِي كَلامِهِ؟ إِنَّ لِلْجَاهِلِ رَجَاءً فِي الإِصْلاحِ أَكْثَرَ مِنْهُ. 21مَنْ دَلَّلَ عَبْدَهُ فِي حَدَاثَتِهِ، يَتَمَرَّدُ عَلَيْهِ فِي النِّهَايَةِ. 22الإِنْسَانُ الْغَضُوبُ يُثِيرُ النِّزَاعَ، وَالرَّجُلُ السَّخُوطُ كَثِيرُ الْمَعَاصِي. 23كِبْرِيَاءُ الإِنْسَانِ تَحُطُّ مِنْ قَدْرِهِ، وَالْمُتَوَاضِعُ الرُّوحِ يُحْرِزُ كَرَامَةً. 24شَرِيكُ اللِّصِّ يَمْقُتُ نَفْسَهُ، يَسْمَعُ اللَّعْنَةَ وَيَكْتُمُ الْجَرِيمَةَ. 25الْخَشْيَةُ مِنَ النَّاسِ فَخٌّ مَنْصُوبٌ، أَمَّا الْمُتَّكِلُ عَلَى الرَّبِّ فَآمِنٌ. 26كَثِيرُونَ يَلْتَمِسُونَ رِضَى الْمُتَسَلِّطِ، إِنَّمَا مِنَ الرَّبِّ يَصْدُرُ قَضَاءُ كُلِّ إِنْسَانٍ. 27الرَّجُلُ الظَّالِمُ مَكْرَهَةٌ لِلصِّدِّيقِ، وَذُو السَّبِيلِ الْمُسْتَقِيمِ رِجْسٌ عِنْدَ الشِّرِّيرِ.