ምሳሌ 27 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 27:1-27

1ነገ በሚሆነው አትመካ፤

ቀን የሚያመጣውን አታውቅምና።

2ሌላው ያመስግንህ እንጂ የገዛ አፍህ አይደለም፤

ሌላ ሰው ያወድስህ እንጂ የገዛ ከንፈርህ አይሁን።

3ድንጋይ ይከብዳል፤ አሸዋም ሸክም ነው፤

የተላላ ሰው ጕነጣ ግን ከሁለቱም ይከብዳል።

4ንዴት ጨካኝ፣ ቍጣም ጐርፍ ነው፤

በቅናት ፊት ግን ማን መቆም ይችላል?

5የተገለጠ ዘለፋ፣

ከተደበቀ ፍቅር ይሻላል።

6ከጠላት ደጋግሞ መሳም ይልቅ፣

የወዳጅ ማቍሰል ይታመናል።

7ለጠገበ ማር አይጥመውም፤

ለተራበ ግን እሬት እንኳ ይጣፍጠዋል።

8ከቤቱ ወጥቶ የሚባዝን ሰው፣

ጎጆዋን ለቅቃ እንደምትባዝን ወፍ ነው።

9ሽቱና ዕጣን ልብን ደስ ያሰኛሉ፤

የወዳጅ ማስደሰትም ከቅን ምክሩ ይመነጫል።

10የራስህንም ሆነ የአባትህን ወዳጅ አትተው፤

መከራ በሚያጋጥምህ ጊዜ ወደ ወንድምህ ቤት አትሂድ፤

ሩቅ ካለ ወንድም ቅርብ ያለ ጎረቤት ይሻላል።

11ልጄ ሆይ፤ ጠቢብ ሁን፤ ልቤን ደስ አሰኘው፤

ለሚንቁኝ ሁሉ መልስ መስጠት እችል ዘንድ።

12ጥንቁቅ አደጋን አይቶ ይሸሸጋል፤

ማስተዋል የጐደለው ግን ወደዚያው ይሄዳል፤ ይጐዳልም።

13ለማይታወቅ ሰው የተዋሰን ልብሱን ግፈፈው፤

ለዘልዛላ ሴት ከተዋሰማ ዐግተው።

14ሰው ድምፁን ከፍ አድርጎ ባልንጀራውን በማለዳ ቢመርቅ፣

እንደ ርግማን ይቈጠራል።

15ጨቅጫቃ ሚስት፣

በዝናብ ቀን እንደሚወርድ የማያቋርጥ ጠፈጠፍ ናት፤

16እርሷን ለመግታት መሞከር፣ ነፋስን እንደ መግታት ወይም ዘይትን

በእጅ እንደ መጨበጥ ነው።

17ብረት ብረትን እንደሚስል፣

ሰውም ሌላውን ሰው እንደዚሁ ይስለዋል።

18በለስን የሚንከባከብ ፍሬዋን ይበላል፤

ጌታውን የሚያገለግልም ክብርን ይጐናጸፋል።

19ውሃ ፊትን እንደሚያሳይ፣

የሰውም ልብ ማንነቱን ገልጦ ያሳያል።

20ሲኦልና የሙታን ዓለም27፥20 ወይም ሞትና ጥፋት እንደማይጠግቡ ሁሉ፣

የሰውም ዐይን አይረካም።

21ብር በማቅለጫ፣ ወርቅ በከውር እንደሚፈተን፣

ሰውም በሚቀበለው ምስጋና ይፈተናል።

22ጅልን በሙቀጫ ብትወቅጠው፣

እንደ እህልም በዘነዘና ብታደቅቀው፣

ጅልነቱን ልታስወግድለት አትችልም።

23በጎችህ በምን ሁኔታ እንዳሉ ደኅና አድርገህ ዕወቅ፤

መንጋህንም ተንከባከብ፤

24ሀብት ለዘላለም አይኖርምና፤

ዘውድም ከትውልድ ወደ ትውልድ ጸንቶ አይኖርም።

25ደረቁ ሣር ተወግዶ፣ አዲሱ ብቅ ሲል፣

በየኰረብታው ላይ ያለው ሣር ተሰብስቦ ሲገባ፣

26ከበግ ጠቦቶች ልብስ ታገኛለህ፤

ፍየሎችም የዕርሻ መሬት መግዣ ይሆኑሃል።

27አንተንና ቤተ ሰብህን፣

ገረዶችህንም ጭምር ለመመገብ፣

የተትረፈረፈ የፍየል ወተት ይኖርሃል።

Ketab El Hayat

الأمثال 27:1-27

1لَا تَتَبَاهَ بِالْغَدِ لأَنَّكَ لَا تَدْرِي مَاذَا يَلِدُ الْيَوْمُ. 2لِيُثْنِ عَلَيْكَ سِوَاكَ لَا فَمُكَ؛ لِيَمْدَحْكَ الْغَرِيبُ لَا شَفَتَاكَ. 3الْحَجَرُ ثَقِيلٌ، وَحُمُولَةُ الرَّمْلِ مُرْهِقَةٌ، وَلَكِنَّ غَضَبَ الْجَاهِلِ أَثْقَلُ مِنْهُمَا. 4الْغَضَبُ فَظٌّ، وَالسَّخَطُ قَهَّارٌ، وَلَكِنْ مَنْ يَصْمُدُ أَمَامَ الْغَيْرَةِ؟ 5التَّوْبِيخُ الظَّاهِرُ خَيْرٌ مِنَ الْحُبِّ الْمُضْمَرِ. 6أَمِينَةٌ هِيَ جُرُوحُ الْمُحِبِّ، وَخَادِعَةٌ هِيَ قُبْلاتُ الْعَدُوِّ 7النَّفْسُ الشَّبْعَانَةُ تَطَأُ الشَّهْدَ، أَمَّا النَّفْسُ الْجَائِعَةُ فَتَجِدُ كُلَّ مُرٍّ حُلْواً. 8الشَّارِدُ عَنْ مَوْطِنِهِ، كَالْعُصْفُورِ الشَّارِدِ عَنْ عُشِّهِ. 9الطِّيبُ وَالْبَخُورُ يُفْرِحَانِ الْقَلْبَ، وَمَسَرَّةُ الصِّدِّيقِ نَاجِمَةٌ عَنِ الْمَشُورَةِ الْمُخْلِصَةِ. 10لَا تَتَخَلَّ عَنْ صَدِيقِكَ وَعَنْ صَدِيقِ أَبِيكَ، وَلا تَذْهَبْ إِلَى بَيْتِ قَرِيبِكَ فِي يَوْمِ بُؤْسِكَ، وَجَارٌ قَرِيبٌ خَيْرٌ مِنْ أَخٍ بَعِيدٍ.

11كُنْ حَكِيماً يَا ابْنِي، وَفَرِّحْ قَلْبِي، فَأَرُدَّ عَلَى مُعَيِّرِيَّ وَأُفْحِمَهُمْ. 12ذُو الْبَصِيرَةِ يَرَى الشَّرَّ فَيَتَوَارَى، أَمَّا الْحَمْقَى فَيَتَقَدَّمُونَ وَيُقَاسُونَ مِنْهُ. 13خُذْ ثَوْبَ مَنْ كَفَلَ الْغَرِيبَ، وَرَهْناً مِمَّنْ ضَمِنَ الأَجْنَبِيَّ. 14مَنْ يُبَارِكُ جَارَهُ فِي الصَّبَاحِ الْمُبَكِّرِ بِصَوْتٍ مُرْتَفِعٍ، تُحْسَبُ بَرَكَتُهُ لَعْنَةً. 15قَطَرَاتُ الْمَطَرِ الْمُتَتَابِعَةُ فِي يَوْمٍ مُمْطِرٍ، وَالْمَرْأَةُ الْمُشَاكِسَةُ سِيَّانِ، 16مَنْ يَكْبَحُ جُمُوحَهَا كَمَنْ يَكْبَحُ الرِّيحَ، أَوْ كَمَنْ يَقْبِضُ عَلَى زَيْتٍ بِيَمِينِهِ.

17كَمَا يَصْقُلُ الْحَدِيدُ الْحَدِيدَ، هَكَذَا يَصْقُلُ الإِنْسَانُ صَاحِبَهُ. 18مَنْ يَرْعَى تِينَةً يَأْكُلُ مِنْ ثَمَرِهَا، وَمَنْ يُرَاعِي سَيِّدَهُ يَحْظَى بِالإِكْرَامِ. 19كَمَا يَعْكِسُ الْمَاءُ صُورَةَ الْوَجْهِ، كَذَلِكَ يَعْكِسُ قَلْبُ الإِنْسَانِ جَوْهَرَهُ. 20كَمَا أَنَّ الْهَاوِيَةَ وَالْهَلاكَ لَا يَشْبَعَانِ، هَكَذَا لَا تَشْبَعُ عَيْنَا الإِنْسَانِ. 21الْبَوْتَقَةُ لِتَنْقِيَةِ الْفِضَّةِ، وَالأَتُونُ لِتَمْحِيصِ الذَّهَبِ، وَالإِنْسَانُ يُحْكَمُ عَلَيْهِ بِمَوْقِفِهِ مِمَّا يُكَالُ لَهُ مِنْ مَدِيحٍ. 22لَوْ دَقَقْتَ الأَحْمَقَ بِمِدَقٍّ فِي هَاوُنٍ مَعَ السَّمِيذِ، فَلَنْ تَبْرَحَ عَنْهُ حَمَاقَتُهُ. 23اجْتَهِدْ فِي مَعْرِفَةِ أَحْوَالِ غَنَمِكَ، وَاحْرِصْ كُلَّ الْحِرْصِ عَلَى قُطْعَانِكَ. 24لأَنَّ الْغِنَى لَا يَدُومُ إِلَى الأَبَدِ، وَلا يَخْلُدُ التَّاجُ مَدَى الدُّهُورِ. 25عِنْدَمَا يَضْمَحِلُّ الْعُشْبُ، وَيَنْمُو الْحَشِيشُ الْجَدِيدُ وَيُجْمَعُ كَلَأُ الْجِبَالِ، 26فَإِنَّ الحُمْلانَ تُوَفِّرُ لَكَ كِسَاءَكَ، وَتَكُونُ الْجِدَاءُ ثَمَناً لِحَقْلِكَ. 27وَيَكُونُ لَكَ مِنْ لَبَنِ الْمَاعِزِ قُوتٌ يَكْفِيكَ، وَطَعَامٌ لأَهْلِ بَيْتِكَ وَغِذَاءٌ لِجَوَارِيكَ.