ምሳሌ 25 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 25:1-28

የሰሎሞን ተጨማሪ ምሳሌዎች

1እነዚህ የይሁዳ ንጉሥ የሕዝቅያስ ሰዎች የቀዷቸው ሌሎች የሰሎሞን ምሳሌዎች ናቸው፦

2ነገርን መሰወር ለእግዚአብሔር ክብሩ ነው፤

ነገርን ፈልፍሎ ማውጣት ግን ለነገሥታት ክብራቸው ነው።

3ሰማያት ከፍ ያሉ እንደ ሆኑ፣ ምድርም ጥልቅ እንደ ሆነች ሁሉ፣

የነገሥታትም ልብ እንደዚሁ አይመረመርም።

4ከብር ዝገትን አስወግድ፤

አንጥረኛውም ንጹሕ ነገር25፥4 ወይም ጽዋ ያገኛል፤

5ክፉን ከንጉሥ ፊት አርቅ፤

ዙፋኑም በጽድቅ ትጸናለች።

6በንጉሥ ፊት ራስህን ከፍ ከፍ አታድርግ፤

በታላላቆች መካከል መገኘትም አይመርህ፤

7በትልቅ ሰው ፊት ከሚያዋርድህ፣

ራሱ፣ “ወደዚህ ከፍ በል” ቢልህ ይሻላልና።

በዐይንህ ያየኸውን ሁሉ፣

8ወደ ፍርድ አደባባይ በችኰላ አታውጣው፤25፥7-8 ወይም ዐይንህን የጣልህበትን የከበረ ሰው፣ 8 …አትውጣ

ባልንጀራህ ካሳፈረህ፣

ኋላ ምን ይውጥሃል?

9ስለ ራስህ ጕዳይ ከባልንጀራህ ጋር በምትከራከርበት ጊዜ፣

የሌላውን ሰው ምስጢር አታውጣ፤

10ያለዚያ ይህን የሚሰማ ያሳፍርሃል፤

አንዴ የጠፋውን ስምህንም ፈጽሞ መመለስ አትችልም።

11ባግባቡ የተነገረ ቃል፣

በብር መደብ ላይ እንደ ተቀረጸ የወርቅ እንኮይ ነው።

12የጠቢብ ሰው ዘለፋ ለሚሰማ ጆሮ፣

እንደ ወርቅ ጕትቻ ወይም እንደ ጥሩ የወርቅ ጌጥ ነው።

13በመከር ጊዜ የበረዶ ቅዝቃዜ ለሰስ እንደሚያደርግ ሁሉ፣

ታማኝ መልእክተኛም ለላኩት እንደዚሁ ነው፤

የጌቶቹን መንፈስ ያሳርፋልና።

14የማይለግሰውን ስጦታ እቸራለሁ ብሎ ጕራ የሚነዛ ሰው፣

ዝናብ እንደሌለው ደመናና ነፋስ ነው።

15በትዕግሥት ገዥን ማግባባት ይቻላል፤

ለስላሳ አንደበትም ዐጥንት ይሰብራል።

16ማር ስታገኝ በልክ ብላ፤

ከበዛ ያስመልስሃል።

17ወደ ባልንጀራህ ቤት እግር አታብዛ፤

ታሰለቸውና ይጠላሃል።

18በባልንጀራው ላይ በሐሰት የሚመሰክር፣

እንደ ቈመጥ፣ እንደ ሰይፍና እንደ ተሳለ ፍላጻ ነው።

19በመከራ ጊዜ በወስላታ ሰው መተማመን፣

በተበላሸ ጥርስና በሰለለ እግር እንደ መታመን ነው።

20ላዘነ ልብ የሚዘምር፣

በብርድ ቀን ልብሱን እንደሚያወልቅ፣

ወይም በሶዳ ላይ እንደ ተጨመረ ሆምጣጤ ነው።

21ጠላትህ ቢራብ አብላው፤

ቢጠማም ውሃ አጠጣው።

22ይህን በማድረግህም፣ በራሱ ላይ ፍም ትከምራለህ፤

እግዚአብሔርም ዋጋህን ይከፍልሃል።

23የሰሜን ነፋስ ዝናብ እንደሚያመጣ ሁሉ፣

ሐሜተኛ ምላስም ቍጡ ፊት ታስከትላለች።

24ከጨቅጫቃ ሚስት ጋር በአንድ ቤት ከመኖር፣

በጣራ ማእዘን ላይ መኖር ይሻላል።

25ከሩቅ የሚመጣ መልካም ዜና፣

የተጠማችን ነፍስ እንደሚያረካ ቀዝቃዛ ውሃ ነው።

26ለክፉ ሰው የሚንበረከክ ጻድቅ፣

እንደ ደፈረሰ ምንጭ ወይም እንደ ተበከለ የጕድጓድ ውሃ ነው።

27ከመጠን በላይ ማር መብላት ጥሩ አይደለም፤

የራስንም ክብር መሻት አያስከብርም።

28ራሱን የማይቈጣጠር ሰው፣

ቅጥሯ እንደ ፈረሰ ከተማ ነው።

New International Version

Proverbs 25:1-28

More Proverbs of Solomon

1These are more proverbs of Solomon, compiled by the men of Hezekiah king of Judah:

2It is the glory of God to conceal a matter;

to search out a matter is the glory of kings.

3As the heavens are high and the earth is deep,

so the hearts of kings are unsearchable.

4Remove the dross from the silver,

and a silversmith can produce a vessel;

5remove wicked officials from the king’s presence,

and his throne will be established through righteousness.

6Do not exalt yourself in the king’s presence,

and do not claim a place among his great men;

7it is better for him to say to you, “Come up here,”

than for him to humiliate you before his nobles.

What you have seen with your eyes

8do not bring25:7,8 Or nobles / on whom you had set your eyes. / 8 Do not go hastily to court,

for what will you do in the end

if your neighbor puts you to shame?

9If you take your neighbor to court,

do not betray another’s confidence,

10or the one who hears it may shame you

and the charge against you will stand.

11Like apples25:11 Or possibly apricots of gold in settings of silver

is a ruling rightly given.

12Like an earring of gold or an ornament of fine gold

is the rebuke of a wise judge to a listening ear.

13Like a snow-cooled drink at harvest time

is a trustworthy messenger to the one who sends him;

he refreshes the spirit of his master.

14Like clouds and wind without rain

is one who boasts of gifts never given.

15Through patience a ruler can be persuaded,

and a gentle tongue can break a bone.

16If you find honey, eat just enough—

too much of it, and you will vomit.

17Seldom set foot in your neighbor’s house—

too much of you, and they will hate you.

18Like a club or a sword or a sharp arrow

is one who gives false testimony against a neighbor.

19Like a broken tooth or a lame foot

is reliance on the unfaithful in a time of trouble.

20Like one who takes away a garment on a cold day,

or like vinegar poured on a wound,

is one who sings songs to a heavy heart.

21If your enemy is hungry, give him food to eat;

if he is thirsty, give him water to drink.

22In doing this, you will heap burning coals on his head,

and the Lord will reward you.

23Like a north wind that brings unexpected rain

is a sly tongue—which provokes a horrified look.

24Better to live on a corner of the roof

than share a house with a quarrelsome wife.

25Like cold water to a weary soul

is good news from a distant land.

26Like a muddied spring or a polluted well

are the righteous who give way to the wicked.

27It is not good to eat too much honey,

nor is it honorable to search out matters that are too deep.

28Like a city whose walls are broken through

is a person who lacks self-control.