ምሳሌ 24 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 24:1-34

1በክፉ ሰዎች አትቅና፤

ጓደኝነታቸውም አይመርህ፤

2ልባቸው ዐመፅን ያውጠነጥናልና፤

ከንፈራቸውም ሸፍጥ ያወራል።

3ቤት በጥበብ ይሠራል፤

በማስተዋልም ይጸናል፤

4በዕውቀትም ውድና ውብ በሆነ ንብረት፣

ክፍሎቹ ይሞላሉ።

5ጠቢብ ሰው ታላቅ ኀይል አለው፤

ዕውቀት ያለውም ሰው ብርታትን ይጨምራል፤

6ጦርነት ለመግጠም መልካም ምክር፣

ድል ለማድረግም ብዙ አማካሪዎች ያስፈልጋሉ።

7ጥበብ ለተላላ በጣም ሩቅ ናት፤

በከተማዪቱ በር ሸንጎ ላይም መናገር አይችልም።

8ክፋት የሚያውጠነጥን፣

“ተንኰለኛ” በመባል ይታወቃል።

9የተላላ ዕቅድ ኀጢአት ነው፤

ሰዎችም ፌዘኛን ይጸየፋሉ።

10በመከራ ጊዜ ፈራ ተባ ካልህ፣

ዐቅምህ ምንኛ ደካማ ነው!

11ወደ ሞት የሚነዱትን ታደጋቸው፤

እየተጐተቱ ለዕርድ የሚሄዱትን አድናቸው።

12አንተም፣ “ስለዚህ ነገር ምንም አላውቅም” ብትል፣

ልብን የሚመረምር እርሱ አያስተውልምን?

ሕይወትህን የሚጠብቃት እርሱ አያውቅምን?

ለእያንዳንዱስ እንደ ሥራው መጠን አይከፍለውምን?

13ልጄ ሆይ፤ መልካም ነውና ማር ብላ፤

የማር ወለላም ጣዕም ይጣፍጥሃል።

14ጥበብም ለነፍስህ እንደዚሁ ጣፋጭ እንደ ሆነች ዕወቅ፤

ብታገኛት ለነገ አለኝታ ይኖርሃል፤

ተስፋህም ከንቱ አይሆንም።

15በጻድቅ ሰው ቤት ላይ እንደ ወንበዴ አታድፍጥ፤

መኖሪያውንም በድንገት አታጥቃ፤

16ጻድቅ ሰባት ጊዜ እንኳ ቢወድቅ ይነሣልና፤

ክፉዎች ግን በጥፋት ይወድቃሉ።

17ጠላትህ ሲወድቅ ደስ አይበልህ፤

ሲሰናከልም ልብህ ሐሤት አያድርግ፤

18አለዚያ እግዚአብሔር ይህን አይቶ ደስ አይለውም፤

ቍጣውንም ከእርሱ ይመልሳል።

19በጨካኞች ድርጊት አትጨነቅ፤

በክፉዎችም አትቅና፤

20ግፈኛ ተስፋ የለውምና፤

የክፉዎችም መብራት ድርግም ብላ ትጠፋለች።

21ልጄ ሆይ፤ እግዚአብሔርንና ንጉሥን ፍራ፤

ከዐመፀኞችም ጋር አትተባበር፤

22ሁለቱም የሚያመጡት መዓት፤

ምን እንደሚሆን ማን ያውቃል?

ተጨማሪ የጠቢባን ምሳሌዎች

23እነዚህም ደግሞ የጠቢባን ምሳሌዎች ናቸው፦

በዳኝነት አድልዎ ማድረግ ተገቢ አይደለም፤

24በደለኛውን፣ “አንተ ንጹሕ ነህ” የሚለውን፣

ሕዝቦች ይረግሙታል፤ መንግሥታትም ያወግዙታል።

25በደለኛውን፣ “አንተ ጥፋተኛ ነህ” የሚሉት ግን መልካም ነገር ይገጥማቸዋል፤

የተትረፈረፈ በረከትም ይወርድላቸዋል።

26እውነተኛ መልስ መስጠት፣

ከንፈርን እንደ መሳም ነው።

27በደጅ ያለውን ሥራህን ፈጽም፤

ዕርሻህን አዘጋጅ፤

ከዚያም በኋላ ቤትህን ሥራ።

28በባልንጀራህ ላይ ያለ ምክንያት አትመስክር፤

በከንፈርህም አትሸንግል።

29“በእኔ ላይ እንደ ሠራብኝ እሠራለታለሁ፤

ስለ አድራጎቱም የእጁን እመልስለታለሁ” አትበል።

30በሰነፍ ሰው ዕርሻ በኩል ዐለፍሁ፤

ማስተዋል የጐደለውን ሰው የወይን ቦታ ዐልፌ ሄድሁ፤

31በያለበት እሾኽ በቅሎበታል፤

መሬቱም ዐረም ለብሷል፤

ቅጥሩም ፈራርሷል።

32ያየሁትን ነገር አወጣሁ፣ አወረድሁ፤

ካስተዋልሁትም ትምህርት አገኘሁ፤

33“ጥቂት ላንቀላፋ፣ ጥቂት ላሸልብ፣

እጄን አጣጥፌ ጥቂት ልረፍ” ብትል፣

34ድኽነት እንደ ወንበዴ፣

ዕጦትም እንደ ታጠቀ ሰው ይመጣብሃል።24፥34 ወይም እንደ ቦዘኔ ወይም ዕጦትም እንደ ለማኝ

Ketab El Hayat

الأمثال 24:1-34

القول العشرون

1لَا تَحْسِدْ أَهْلَ الشَّرِّ، وَلا تَشْتَهِ مُعَاشَرَتَهُمْ، 2لأَنَّ قُلُوبَهُمْ تَتَآمَرُ عَلَى ارْتِكَابِ الظُّلْمِ، وَأَلْسِنَتَهُمْ تَنْطِقُ بِالإِسَاءَةِ.

القول الحادي والعشرون

3بِالْحِكْمَةِ يُبْنَى الْبَيْتُ، وَبِالْفَهْمِ يَرْسَخُ. 4بِالْمَعْرِفَةِ تَكْتَظُّ الْحُجْرَاتُ بِكُلِّ نَفِيسٍ، وَكُنُوزٍ نَادِرَةٍ.

القول الثاني والعشرون

5الرَّجُلُ الْحَكِيمُ يَتَمَتَّعُ بِالْعِزَّةِ، وَذُو الْمَعْرِفَةِ يَزْدَادُ قُوَّةً، 6لأَنَّكَ بِحُسْنِ التَّدْبِيرِ تَخُوضُ حَرْبَكَ، وَبِكَثْرَةِ الْمُشِيرِينَ يَكُونُ الْخَلاصُ.

القول الثالث والعشرون

7الْحِكْمَةُ أَسْمَى مِنْ أَنْ يُدْرِكَهَا الْجَاهِلُ، وَفِي سَاحَةِ الْمَدِينَةِ لَا يَفْتَحُ فَاهُ!

القول الرابع والعشرون

8الْمُتَفَكِّرُ فِي ارْتِكَابِ الشَّرِّ يُدْعَى مُتَآمِراً. 9نَوَايَا الْجَاهِلِ خَطِيئَةٌ، وَالْمُسْتَهْزِئُ رِجْسٌ عِنْدَ النَّاسِ.

القول الخامس والعشرون

10إِنْ عَيِيتَ فِي يَوْمِ الضِّيقِ تَكُونُ وَاهِنَ الْقُوَى. 11أَنْقِذِ الْمَسُوقِينَ إِلَى الْمَوْتِ وَرُدَّ الْمُتَعَثِّرِينَ الذَّاهِبِينَ إِلَى الذَّبْحِ. 12إِنْ قُلْتَ: إِنَّنَا لَمْ نَعْرِفْ هَذَا، أَفَلا يَفْهَمُ هَذَا وَازِنُ الْقُلُوبِ؟ أَلا يُدْرِكُهُ رَاعِي النُّفُوسِ، فَيُجَازِيَ الإِنْسَانَ بِمُقْتَضَى عَمَلِهِ؟

القول السادس والعشرون

13يَا ابْنِي، كُلْ عَسَلاً لأَنَّهُ طَيِّبٌ، وَكَذَلِكَ الشَّهْدَ لأَنَّهُ حُلْوٌ لِمَذَاقِكَ. 14لِذَلِكَ الْتَمِسِ الْحِكْمَةَ لِنَفْسِكَ، فَإِذَا وَجَدْتَهَا تَحْظَى بِالثَّوَابِ وَلا يَخِيبُ رَجَاؤُكَ.

القول السابع والعشرون

15لَا تَكْمُنْ كَمَا يَكْمُنُ الشِّرِّيرُ لِمَسْكَنِ الصِّدِّيقِ وَلا تُدَمِّرْ مَنْزِلَهُ، 16لأَنَّ الصِّدِّيقَ يَسْقُطُ سَبْعَ مَرَّاتٍ، وَمَعَ ذَلِكَ يَنْهَضُ، أَمَّا الأَشْرَارُ فَيَتَعَثَّرُونَ بِالشَّرِّ.

القول الثامن والعشرون

17لَا تَشْمَتْ لِسُقُوطِ عَدُوِّكَ، وَلا يَبْتَهِجْ قَلْبُكَ إِذَا عَثَرَ، 18لِئَلّا يَشْهَدَ الرَّبُّ، فَيَسُوءَ الأَمْرُ فِي عَيْنَيْهِ وَيَصْرِفَ غَضَبَهُ عَنْهُ.

القول التاسع والعشرون

19لَا يَتَآكَلْ قَلْبُكَ غَيْظاً مِنْ فَاعِلِي الإِثْمِ، وَلا تَحْسِدِ الأَشْرَارَ، 20إِذْ لَا ثَوَابَ لِلشِّرِّيرِ، وَسِرَاجُهُ يَنْطَفِئُ.

القول الثلاثون

21يَا ابْنِي اتَّقِ الرَّبَّ وَالْمَلِكَ، وَلا تُعَاشِرِ الْمُتَقَلِّبِينَ، 22لأَنَّ هَذَيْنِ الاثْنَيْنِ يُنْزِلانِ الْبَلِيَّةَ بَغْتَةً عَلَيْهِمْ. وَمَنْ يَدْرِي أَيَّةَ كَوَارِثَ تَصْدُرُ عَنْهُمَا؟

أقوال حكمة أخرى

23وَهَذِهِ أَيْضاً أَقْوَالُ الْحُكَمَاءِ: التَّحَيُّزُ فِي الْحُكْمِ مُشِينٌ، 24وَمَنْ يَقُولُ لِلشِّرِّيرِ: أَنْتَ بَرِيءٌ، تَلْعَنُهُ الشُّعُوبُ وَتَمْقُتُهُ الأُمَمُ. 25أَمَّا الَّذِينَ يُوَبِّخُونَهُ فَلَهُمُ الْغِبْطَةُ وَتَحُلُّ عَلَيْهِمْ بَرَكَةُ الْخَيْرِ. 26مَنْ يُجِيبُ بِقَوْلٍ صَائِبٍ يَحْظَى بِالْكَرَامَةِ. 27أَنْجِزْ عَمَلَكَ فِي الْخَارِجِ وَهَيِّئْ حَقْلَكَ لِنَفْسِكَ، ثُمَّ ابْنِ بَيْتَكَ. 28لَا تَشْهَدْ ضِدَّ قَرِيبِكَ مِنْ غَيْرِ دَاعٍ، فَلِمَاذَا تَنْطِقُ شَفَتَاكَ زُوراً؟ 29لَا تَقُلْ: سَأُعَامِلُهُ بِمِثْلِ مَا عَامَلَنِي، وَأُجَازِيهِ عَلَى مَا ارْتَكَبَهُ فِي حَقِّي.

30اجْتَزْتُ فِي حَقْلِ الْكَسُولِ وَبِكَرْمِ الرَّجُلِ الْفَاقِدِ الْبَصِيرَةِ، 31وَإذَا بِالشَّوْكِ قَدْ كَسَاهُ، وَالْعَوْسَجِ قَدْ غَطَّى كُلَّ أَرْضِهِ، وَجِدَارِ حِجَارَتِهِ قَدِ انْهَارَ، 32فَاعْتَبَرَ قَلْبِي بِمَا شَاهَدْتُ، وَتَلَقَّنْتُ دَرْساً مِمَّا رَأَيْتُ. 33أَدْرَكْتُ أَنَّ قَلِيلاً مِنَ النُّعَاسِ بَعْدَ قَلِيلٍ مِنَ النَّوْمِ، وَطَيَّ الْيَدَيْنِ لِلْهُجُوعِ، 34تَجْعَلُ الْفَقْرَ يُقْبِلُ عَلَيْكَ كَقَاطِعِ طَرِيقٍ وَالْعَوَزَ كَغَازٍ مُسَلَّحٍ!