ምሳሌ 23 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 23:1-35

1ከገዥ ጋር ለመብላት በምትቀመጥበት ጊዜ፣

በፊትህ ያለውን በሚገባ23፥1 ወይም ማን መሆኑን አስተውል፤

2ስግብግብም ብትሆን እንኳ፣

በጕረሮህ ላይ ካራ አጋድምበት፤

3የእርሱ ጣፋጭ መብል አያስጐምጅህ፤

ምግቡ አታላይ ነውና።

4ሀብት ለማግኘት ስትል ራስህን አታድክም፤

ሐሳብህን የመግታት ጥበብ ይኑርህ።

5በሀብት ላይ ዐይንህን ብትጥል፣

ወዲያው ይጠፋል፤

ወደ ሰማይ እንደሚበርር ንስር፣ በርግጥ ክንፍ አውጥቶ ይበርራል።

6የሥሥታምን ምግብ አትብላ፤

ጣፋጭ መብሉም አያስጐምጅህ፤

7ሁልጊዜ ስለ ዋጋ የሚያሰላ ሰው ነውና፤23፥7 ወይም በልቡ እንዳሰበ እንዲሁ ነውና ወይም ግብዣ አዘጋጅቶ

“ብላ፣ ጠጣ” ይልሃል፤

ልቡ ግን ከአንተ ጋር አይደለም።

8የበላሃት ትንሿ እንኳ ታስመልስሃለች፤

የምስጋና ቃልህንም ከንቱ ታደርጋለህ።

9ከጅል ጋር አትነጋገር፤

የቃልህን ጥበብ ያንኳስሳልና።

10የጥንቱን የወሰን ምልክት አታፋልስ፤

አባት የሌላቸውንም ልጆች መሬት አትግፋ፤

11ታዳጊያቸው ብርቱ ነውና፤

እርሱ ይፋረድላቸዋል።

12ልብህን ለምክር፣

ጆሮህንም ለዕውቀት ቃል ስጥ።

13ልጅን ከመቅጣት ወደ ኋላ አትበል፤

በአርጩሜ ብትገርፈው አይሞትም።

14በአርጩሜ ቅጣው፤

ነፍሱንም ከሞት23፥14 ዕብራይስጡ ሲኦል ይላል አድናት።

15ልጄ ሆይ፤ ልብህ ጠቢብ ቢሆን፣

የእኔም ልብ ሐሤት ያደርጋል፤

16ከንፈሮችህ ትክክሉን ቢናገሩ፣

ውስጣዊ ሁለንተናዬ ሐሤት ያደርጋል።

17ልብህ በኀጢአተኞች አይቅና፤

ነገር ግን ዘወትር እግዚአብሔርን ለመፍራት ትጋ።

18ለነገ ርግጠኛ አለኝታ ይኖርሃል፤

ተስፋህም ከንቱ አይሆንም።

19ልጄ ሆይ አድምጥ፤ ጠቢብም ሁን፤

ልብህም ከትክክለኛው መንገድ አይውጣ።

20ብዙ የወይን ጠጅ ከሚጠጡ፣

ሥጋ ከሚሰለቅጡ ጋር አትወዳጅ፤

21ሰካራሞችና ሆዳሞች ድኾች ይሆናሉና፤

እንቅልፋምነትም ቡትቶ ያለብሳቸዋል።

22የወለደህን አባትህን አድምጥ፤

እናትህንም ባረጀች ጊዜ አትናቃት።

23እውነትን ግዛት እንጂ አትሽጣት፤

ጥበብን፣ ተግሣጽንና ማስተዋልን ገንዘብህ አድርግ።

24የጻድቅ ሰው አባት እጅግ ደስ ይለዋል፤

ጠቢብ ልጅ ያለውም በእርሱ ሐሤት ያደርጋል።

25አባት እናትህ ደስ ይበላቸው፤

ወላጅ እናትህም ሐሤት ታድርግ።

26ልጄ ሆይ፤ ልብህን ስጠኝ፤

ዐይኖችህም ከመንገዴ አይውጡ፤

27ዘልዛላ ሚስት ጠባብ ጕድጓድ፣

አመንዝራም ሴት ዐዘቅት ናትና፤

28እንደ ወንበዴ ታደባለች፤

በሰዎችም መካከል ወስላቶችን ታበዛለች።

29ዋይታ የማን ነው? ሐዘንስ የማን ነው?

ጠብ የማን ነው? ብሶትስ የማን ነው?

በከንቱ መቍሰል የማን ነው? የዐይን ቅላትስ የማን ነው?

30የወይን ጠጅ በመጠጣት ጊዜያቸውን ለሚያባክኑ ነው፤

እየዞሩ ድብልቅ የወይን ጠጅ ለሚቀማምሱ ሰዎች ነው።

31መልኩ ቀይ ሆኖ፣

በብርጭቆ ውስጥ ሲያንጸባርቅ፣

ሰተት ብሎ በሚወርድበትም ጊዜ፣ ወደ ወይን ጠጅ ትክ ብለህ አትመልከት።

32በመጨረሻው እንደ እባብ ይነድፋል፤

እንደ እፉኝትም መርዙን ይረጫል።

33ዐይኖችህ እንግዳ ነገር ያያሉ፤

አእምሮህም ይቀባዥራል።

34በባሕር ላይ የተኛህ፣

በመርከብ ምሰሶ ጫፍ ላይ የተጋደምህ ትመስላለህ።

35አንተም፣ “መቱኝ፤ አልተጐዳሁም፤

ደበደቡኝ፤ አልተሰማኝም፤

ታዲያ፣ ሌላ መጠጥ እንዳገኝ፣

መቼ ነው የምነቃው?” ትላለህ።

Ketab El Hayat

الأمثال 23:1-35

القول السابع

1إِذَا جَلَسْتَ تَأْكُلُ مَعَ حَاكِمٍ، فَتَأَمَّلْ أَشَدَّ التَّأَمُّلِ فِيمَا هُوَ أَمَامَكَ. 2ضَعْ سِكِّيناً فِي حَلْقِكَ إِنْ كُنْتَ شَرِهاً! 3لَا تَشْتَهِ أَطَايِبَهُ لأَنَّهَا أَطْعِمَةٌ خَادِعَةٌ.

القول الثامن

4لَا تَشْقَ طَلَباً للثَّرَاءِ. اكْبَحْ جِمَاحَ نَفْسِكَ بِفَضْلِ فِطْنَتِكَ. 5مَا تَكَادُ تَتَأَلَّقُ عَيْنَاكَ حُبُوراً بِهِ حَتَّى يَتَبَدَّدَ، إِذْ فَجْأَةً يَصْنَعُ لِنَفْسِهِ أَجْنِحَةً وَيَطِيرُ كَالنَّسْرِ مُحَلِّقاً نَحْوَ السَّمَاءِ.

القول التاسع

6لَا تَأْكُلْ مِنْ خُبْزِ رَجُلٍ بَخِيلٍ، وَلا تَشْتَهِ أَطَايِبَهُ، 7لأَنَّهُ يُفَكِّرُ دَائِماً فِي الثَّمَنِ. يَقُولُ لَكَ: كُلْ وَاشْرَبْ، إِلّا أَنَّ قَلْبَهُ يَكُنُّ لَكَ غَيْرَ ذَلِكَ، 8فَتَتَقَيَّأَ اللُّقَمَ الَّتِي أَكَلْتَهَا وَتَذْهَبَ كَلِمَاتُكَ الطَّيِّبَةُ سُدىً!

القول العاشر

9لَا تَتَكَلَّمْ فِي مَسَامِعِ الْجَاهِلِ لأَنَّهُ يَزْدَرِي بِحِكْمَةِ أَقْوَالِكَ.

القول الحادي عشر

10لَا تَنْقُلْ مَعَالِمَ تُخْمٍ قَدِيمٍ، وَلا تَدْخُلْ حُقُولَ الأَيْتَامِ، 11لأَنَّ وَلِيَّهُمْ قَادِرٌ، وَهُوَ يُدَافِعُ عَنْ دَعْوَاهُمْ ضِدَّكَ.

القول الثاني عشر

12وَجِّهْ قَلْبَكَ إِلَى التَّأْدِيبِ، وَأَرْهِفْ أُذُنَيْكَ لِكَلِمَاتِ الْمَعْرِفَةِ.

القول الثالث عشر

13لَا تَمْتَنِعْ عَنْ تَأْدِيبِ الْوَلَدِ. إِنْ عَاقَبْتَهُ بِالْعَصَا لَا يَمُوتُ. 14اضْرِبْهُ بِالْعَصَا، فَتُنْقِذَ نَفْسَهُ مِنَ الْهَاوِيَةِ.

القول الرابع عشر

15يَا ابْنِي إِنْ كَانَ قَلْبُكَ حَكِيماً، يَبْتَهِجُ قَلْبِي أَيْضاً، 16تَفْرَحُ نَفْسِي عِنْدَمَا تَنْطِقُ شَفَتَاكَ بِالْحَقِّ.

القول الخامس عشر

17لَا يَغَرْ قَلْبُكَ مِنَ الْخُطَاةِ، بَلْ وَاظِبْ عَلَى تَقْوَى الرَّبِّ الْيَوْمَ كُلَّهُ، 18فَهُنَاكَ حَقّاً ثَوَابٌ، وَرَجَاؤُكَ لَنْ يَخِيبَ.

القول السادس عشر

19اسْتَمِعْ يَا ابْنِي وَكُنْ حَكِيماً، وَوَجِّهْ قَلْبَكَ نَحْوَ سَبِيلِ الْحَقِّ. 20لَا تَكُنْ وَاحِداً مِنْ مُدْمِنِي الْخَمْرِ، الشَّرِهِينَ لاِلْتِهَامِ اللَّحْمِ، 21لأَنَّ السِّكِّيرَ وَالشَّرِهَ يَفْتَقِرَانِ، وَكَثْرَةُ النَّوْمِ تَكْسُو الْمَرْءَ بِالْخِرَقِ.

القول السابع عشر

22اسْتَمِعْ لأَبِيكَ الَّذِي أَنْجَبَكَ، وَلا تَحْتَقِرْ أُمَّكَ إِذَا شَاخَتْ. 23اقْتَنِ الْحَقَّ وَلا تَبِعْهُ، وَكَذَا الْحِكْمَةَ وَالتَّأْدِيبَ وَالْفِطْنَةَ. 24أَبُو الصِّدِّيقِ يَغْتَبِطُ أَشَدَّ الاغْتِبَاطِ، وَمَنْ أَنْجَبَ حَكِيماً يُسَرُّ بِهِ. 25لِيَفْرَحْ أَبُوكَ وَأُمُّكَ وَلْتَبْتَهِجْ مَنْ أَنْجَبَتْكَ.

القول الثامن عشر

26يَا ابْنِي هَبْنِي قَلْبَكَ، وَلْتُرَاعِ عَيْنَاكَ سُبُلِي. 27فَإِنَّ الْعَاهِرَةَ حُفْرَةٌ عَمِيقَةٌ، وَالزَّوْجَةَ الْمَاجِنَةَ بِئْرٌ ضَيِّقَةٌ، 28تَكْمُنُ مُتَرَبِّصَةً كَلِصٍّ، وَتَزِيدُ مِنَ الْغَادِرِينَ بَيْنَ النَّاسِ.

القول التاسع عشر

29لِمَنِ الْمُعَانَاةُ؟ لِمَنِ الْوَيْلُ وَالشَّقَاءُ وَالْمُخَاصَمَاتُ وَالشَّكْوَى؟ لِمَنِ الْجِرَاحُ بِلا سَبَبٍ؟ وِلِمَنِ احْمِرَارُ الْعَيْنَيْنِ؟ 30إِنَّهَا لِلْمُدْمِنِينَ الْخَمْرَ، السَّاعِينَ وَرَاءَ الْمُسْكِرِ الْمَمْزُوجِ. 31لَا تَنْظُرْ إِلَى الْخَمْرِ إِذَا الْتَهَبَتْ بِالاحْمِرَارِ، وَتَأَلَّقَتْ فِي الْكَأْسِ، وَسَالَتْ سَائِغَةً، 32فَإِنَّهَا فِي آخِرِهَا تَلْسَعُ كَالْحَيَّةِ وَتَلْدَغُ كَالأُفْعُوَانِ. 33فَتُشَاهِدُ عَيْنَاكَ أُمُوراً غَرِيبَةً، وَقَلْبُكَ يُحَدِّثُكَ بِأَشْيَاءَ مُلْتَوِيَةٍ، 34فَتَكُونُ مُتَرَنِّحاً كَمَنْ يَضْطَجِعُ فِي وَسَطِ عُبَابِ الْبَحْرِ، أَوْ كَرَاقِدٍ عَلَى قِمَّةِ سَارِيَةٍ! 35فَتَقُولُ: «ضَرَبُونِي وَلَكِنْ لَمْ أَتَوَجَّعْ. لَكَمُونِي فَلَمْ أَشْعُرْ، فَمَتَى أَسْتَيْقِظُ؟ سَأَذْهَبُ أَلْتَمِسُ شُرْبَهَا مَرَّةً أُخْرَى».