ምሳሌ 2 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 2:1-22

ከጥበብ የሚገኝ በረከት

1ልጄ ሆይ፤ ቃሌን ብትቀበል፣

ትእዛዜንም በልብህ ብታኖር፣

2ጆሮህን ወደ ጥበብ ብታቀና፣

ልብህንም ወደ ማስተዋል ብትመልስ፣

3እንዲሁም የመለየት ጥበብን ብትማጠን፣

ድምፅህን ከፍ አድርገህ ማስተዋልን ብትጣራ፣

4እርሷንም እንደ ብር ብትፈልጋት፣

እንደ ተሸሸገ ሀብት አጥብቀህ ብትሻት፣

5በዚያን ጊዜ ፈሪሀ እግዚአብሔርን ትረዳለህ፤

አምላክንም ማወቅ ታገኛለህ።

6እግዚአብሔር ጥበብን ይሰጣልና፤

ከአንደበቱም ዕውቀትና ማስተዋል ይወጣል።

7እርሱ ለቅኖች ድልን ያከማቻል፤

ያለ ነቀፋ ለሚሄዱትም ጋሻ ይሆናቸዋል፤

8የፍትሕን መንገድ ይጠብቃል፤

የታማኞቹንም አካሄድ ያጸናል።

9በዚያን ጊዜ ጽድቅን፣ ፍትሕን፣ ሚዛናዊነትን፣

መልካሙንም መንገድ ሁሉ ትገነዘባለህ፤

10ጥበብ ልብህ ውስጥ ትገባለችና፤

ዕውቀትም ነፍስህን ደስ ታሰኛለች፤

11የመለየት ችሎታ ይጋርድሃል፤

ማስተዋልም ይጠብቅሃል።

12ጥበብ ንግግራቸው ጠማማ ከሆነ ሰዎች፣

ከክፉዎችም መንገድ ታድንሃለች፤

13እነዚህም በጨለማ መንገድ ለመሄድ፣

ቀናውን ጐዳና የሚተዉ ናቸው፤

14ክፉ በመሥራት ደስ የሚላቸው፣

በክፋት ጐዳና ሐሤት የሚያደርጉ፣

15መንገዳቸው ጠማማ፣

በአካሄዳቸው ጠመዝማዞች ናቸው።

16ከአመንዝራ ሴትም ትጠብቅሃለች፤

በአንደበቷም ከምታታልል ዘልዛላ ታድንሃለች፤

17ይህችም የልጅነት ባሏን የተወች፣

በአምላኳ ፊት የገባችውን ኪዳን2፥17 ወይም የአምላኳን ኪዳን ያቃለለች ናት።

18ቤቷ ወደ ሞት ያደርሳል፤

መንገዷም ወደ መናፍስተ ሙታን ያመራል።

19ወደ እርሷ የሚገባ ማንም አይመለስም፤

የሕይወትንም መንገድ አያገኝም።

20አንተም በደጋግ ሰዎች ጐዳና ትሄዳለህ፤

የጻድቃንንም መንገድ ይዘህ ትጓዛለህ።

21ቅኖች በምድሪቱ ይቀመጣሉና፤

ነቀፋ የሌለባቸውም በእርሷ ላይ ጸንተው ይኖራሉ።

22ክፉዎች ግን ከምድሪቱ ይወገዳሉ፤

ታማኝነት የጐደላቸውም ከእርሷ ይነቀላሉ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

箴言 2:1-22

智慧的益处

1孩子啊,

你若接受我的教诲,

珍爱我的诫命,

2侧耳聆听智慧,

倾心渴慕悟性;

3你若呼求洞见,

竭力追求悟性,

4寻它如寻银子,

找它如找宝藏,

5你就会懂得敬畏耶和华,

认识上帝。

6因为耶和华赐人智慧,

知识和悟性出自祂的口。

7祂使正直人充满智慧,

是行为纯全者的盾牌。

8祂看守正义之路,

护卫虔诚人的道。

9这样,你就明白何为仁义、

公平和正直,

懂得一切美善之道。

10因为智慧必进入你心,

知识必令你的灵欢快。

11明辨力必护佑你,

悟性必看顾你。

12智慧必救你远离恶道,

脱离言语荒谬的人。

13他们舍弃正道,走上黑路,

14以行恶为乐,喜爱恶人的邪僻;

15他们的道路歪邪,行径扭曲。

16智慧要救你脱离淫妇,

脱离花言巧语的妓女。

17她撇弃了年轻时的丈夫,

忘了在上帝面前立的约。

18她的家通向死亡,

她的路直达阴间。

19到她那里的人都有去无回,

找不到生命之道。

20所以你要行善人的路,

守义人的道。

21因为在地上,

正直人必安居,

纯全无过的人必长存,

22恶人必遭灭绝,

奸徒必被铲除。