ምሳሌ 18 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 18:1-24

1ወዳጅነትን የማይፈልግ ሰው የራሱን ፍላጎት ብቻ ይከተላል፤

ቅን የሆነውንም ፍርድ ሁሉ ይቃወማል።

2ተላላ ከማስተዋል ርካታን አያገኝም፤

የራሱን ሐሳብ በመግለጥ ግን ደስ ይለዋል።

3ክፋት ስትመጣ ንቀት ትከተላለች፤

ከዕፍረትም ጋር ውርደት ትመጣለች።

4ከሰው አፍ የሚወጡ ቃላት ጥልቅ ውሆች ናቸው፤

የጥበብም ምንጭ እንደሚንዶለዶል ፏፏቴ ነው።

5ለክፉ ሰው ማድላት፣

ንጹሑንም ፍትሕ መንሣት ተገቢ አይደለም።

6የተላላ ከንፈር ጠብ ያመጣበታል፤

አፉም በትር ይጋብዛል።

7ተላላ ሰው አፉ መጥፊያው ነው፤

ከንፈሮቹም ለነፍሱ ወጥመድ ናቸው።

8የሐሜተኛ ቃል እንደ ጣፋጭ ጕርሻ ነው፤

ወደ ሰው ውስጣዊ ክፍል ዘልቆ ይገባል።

9ለሥራው ደንታ የሌለው ሰው፣

የአጥፊ ወንድም ነው።

10የእግዚአብሔር ስም ጽኑ ግንብ ነው፤

ጻድቅ ወደ እርሱ በመሮጥ ተገን ያገኝበታል።

11የባለጠጎች ሀብት የተመሸገ ከተማቸው ነው፤

እንደማይወጣ ረዥም ግንብም ይቈጥሩታል።

12ከውድቀቱ በፊት ሰው ልቡ ይታበያል፤

ትሕትና ግን ክብርን ትቀድማለች።

13ከማዳመጡ አስቀድሞ የሚመልስ፣

ቂልነትና ዕፍረት ይሆንበታል።

14በሕመም ጊዜ፣ ሰውን መንፈሱ ትደግፈዋለች፤

የተሰበረውን መንፈስ ግን ማን ሊሸከም ይችላል?

15የአስተዋይ ልብ ዕውቀትን ይገበያል፤

የጠቢብም ጆሮ አጥብቆ ይሻታል።

16እጅ መንሻ ለሰጪው መንገድ ትከፍትለታለች፤

ታላላቅ ሰዎች ፊትም ታቀርበዋለች።

17አስቀድሞ ጕዳዩን የሚያሰማ ትክክለኛ ይመስላል፤

ይኸውም ባላንጣው መጥቶ እስከሚመረመር ድረስ ነው።

18ዕጣ መጣጣል ሙግትን ያስቆማል፤

ኀይለኛ ባላንጣዎችንም ይገላግላል።

19የተበደለ ወንድም ከተመሸገ ከተማ ይበልጥ የማይበገር ነው፤

ጠቡም እንደ ጠንካራ የግንብ መዝጊያ ነው።

20ሰው በአንደበቱ ፍሬ ሆዱ ይጠግባል፤

በከንፈሩም ምርት ይረካል።

21አንደበት የሞትና የሕይወት ኀይል አላት፤

የሚወድዷትም ፍሬዋን ይበላሉ።

22ሚስት የሚያገኝ መልካም ነገርን ያገኛል፤

ከእግዚአብሔርም ዘንድ ሞገስን ይቀበላል።

23ድኻ በመለማመጥ ምሕረት ይለምናል፤

ሀብታም ግን በማናለብኝነት ይመልሳል።

24ወዳጅ የሚያበዛ ሰው ራሱን ለጥፋት ይዳርጋል፤

ነገር ግን ከወንድም አብልጦ የሚቀርብ ጓደኛም አለ።

Ketab El Hayat

الأمثال 18:1-24

1الْمُعْتَزِلُ (عَنِ اللهِ وَالنَّاسِ) يَنْشُدُ شَهْوَتَهُ وَيَتَنَكَّرُ لِكُلِّ مَشُورَةٍ صَائِبَةٍ. 2لَا يَعْبَأُ الْجَاهِلُ بِالْفِطْنَةِ، بَلْ هَمُّهُ الإِعْرَابُ عَمَّا فِي نَفْسِهِ. 3إِذَا أَقْبَلَ الشِّرِّيرُ أَقْبَلَ مَعَهُ الاحْتِقَارُ، وَالْعَارُ يُلازِمُ الْهَوَانَ. 4كَلِمَاتُ الإِنْسَانِ مِيَاهٌ عَمِيقَةٌ يَتَعَذَّرُ سَبْرُ غَوْرِهَا، وَيَنْبُوعُ الْحِكْمَةِ نَهْرٌ مُتَدَفِّقٌ. 5مِنَ السُّوءِ مُحَابَاةُ الشِّرِّيرِ، أَوْ حِرْمَانُ الْبَرِيءِ مِنَ الْقَضَاءِ الْحَقِّ. 6أَقْوَالُ الْجَاهِلِ تُوْقِعُهُ فِي الْمَتَاعِبِ، وَكَلِمَاتُهُ تُسَبِّبُ لَهُ الضَّرْبَ. 7كَلِمَاتُ الْجَاهِلِ مَهْلَكَةٌ لَهُ، وَأَقْوَالُهُ فَخٌّ لِنَفْسِهِ. 8هَمْسَاتُ النَّمَّامِ كَلُقَمٍ سَائِغَةٍ تَنْزَلِقُ إِلَى بَوَاطِنِ الْجَوْفِ. 9الْمُتَقَاعِسُ عَنْ عَمَلِهِ هُوَ أَخُو الهَادِمِ.

10اسْمُ الرَّبِّ بُرْجٌ مَنِيعٌ يُهْرَعُ إِلَيْهِ الصِّدِّيقُ وَيَنْجُو مِنَ الْخَطَرِ. 11ثَرْوَةُ الْغَنِيِّ مَدِينَتُهُ الْحَصِينَةُ، وَهِيَ فِي وَهْمِهِ سُورٌ شَامِخٌ. 12قَبْلَ الانْكِسَارِ تَشَامُخُ الْقَلْبِ، وَقَبْلَ الْكَرَامَةِ التَّواضُعُ. 13مَنْ أَجَابَ عَنْ أَمْرٍ مَازَالَ يَجْهَلُهُ، فَذَاكَ حَمَاقَةٌ مِنْهُ وَعَارٌ لَهُ. 14رُوحُ الإِنْسَانِ الْقَوِيَّةُ تَحْتَمِلُ مَرَضَهُ، أَمَّا الرُّوحُ الْمُنْسَحِقَةُ فَمَنْ يَتَحَمَّلُهَا؟ 15عَقْلُ الْفَهِيمِ يَقْتَنِي مَعْرِفَةً، وَأُذُنُ الْحُكَمَاءِ تَنْشُدُ عِلْماً. 16هَدِيَّةُ الإِنْسَانِ تُمَهِّدُ لَهُ السَّبِيلَ، وَتَجْعَلُهُ يَمْثُلُ أَمَامَ الْعُظَمَاءِ.

17مَنْ يَعْرِضُ قَضِيَّتَهُ أَوَّلاً يَبْدُو مُحِقّاً إِلَى أَنْ يَأْتِيَ آخَرُ وَيَسْتَجْوِبَهُ. 18تَفْصِلُ الْقُرْعَةُ فِي الْخُصُومَاتِ وَتَحْسِمُ الأَمْرَ بَيْنَ الْمُتَنَازِعِينَ الأَقْوِيَاءِ. 19إِرْضَاءُ الأَخِ الْمُتَأَذِّي أَصْعَبُ مِنْ قَهْرِ مَدِينَةٍ حَصِينَةٍ، وَالْمُخَاصَمَاتُ كَعَارِضَةِ قَلْعَةٍ.

20مِنْ ثَمَرِ أَقْوَالِ الإِنْسَانِ تَشْبَعُ ذَاتُهُ، وَمِنْ غَلَّةِ كَلِمَاتِهِ يَلْقَى جَزَاءَهُ 21فِي اللِّسَانِ حَيَاةٌ أَوْ مَوْتٌ، وَالْمُوْلَعُونَ بِاسْتِخْدَامِهِ يَتَحَمَّلُونَ الْعَوَاقِبَ. 22مَنْ عَثَرَ عَلَى زَوْجَةٍ صَالِحَةٍ نَالَ خَيْراً وَحَظِيَ بِمَرْضَاةِ اللهِ. 23يَتَوَسَّلُ الْفَقِيرُ بِتَضَرُّعَاتٍ، أَمَّا الْغَنِيُّ فَيُجَاوِبُ بِخُشُونَةٍ. 24مَنْ يُكْثِرِ الأَصْحَابَ يُخْرِبْ نَفْسَهُ، وَرُبَّ صَدِيقٍ أَلْزَقُ مِنَ الأَخِ.