ምሳሌ 17 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 17:1-28

1ጠብ እያለ ግብዣ17፥1 ዕብራይስጡ መሥዋዕት ይላል። ከሞላበት ቤት ይልቅ፣

በሰላምና በጸጥታ የእንጀራ ድርቆሽ ይሻላል።

2ጠቢብ አገልጋይ በወራዳ ልጅ ላይ ሥልጣን ይኖረዋል፤

ከወንድማማቾቹም እንደ አንዱ ውርስ ይካፈላል።

3ማቅለጫ ለብር፣ ከውር ለወርቅ ነው፤

እግዚአብሔር ግን ልብን ይመረምራል።

4እኩይ ሰው ክፉ ንግግር ያዳምጣል፤

ሐሰተኛም የተንኰለኛን አንደበት በጥንቃቄ ይሰማል።

5በድኾች የሚያፌዝ ፈጣሪያቸውን ይንቃል፤

በሌላው ሰው መከራ ደስ የሚለው ከቅጣት አያመልጥም።

6የልጅ ልጆች ለአረጋውያን ዘውድ ናቸው፤

ወላጆችም ለልጆቻቸው አለኝታ ናቸው።

7መልካም አነጋገር17፥7 ወይም የኵራት አነጋገር ለተላላ አይሰምርለትም፤

ለገዥማ ሐሰተኛ አንደበት የቱን ያህል የከፋ ይሆን!

8እጅ መንሻ ለሰጭው እንደ ድግምት ዕቃ ነው፤

በሄደበትም ቦታ ሁሉ ይሳካለታል።

9በደልን የሚሸፍን ፍቅርን ያዳብራል፤

ነገርን የሚደጋግም ግን የልብ ወዳጆችን ይለያያል።

10መቶ ግርፋት ተላላን ከሚሰማው ይልቅ፣

ተግሣጽ ለአስተዋይ ጠልቆ ይሰማል።

11ክፉ ሰው ዐመፅን ብቻ ይፈልጋል፤

በእርሱም ላይ ጨካኝ መልእክተኛ ይላክበታል።

12ተላላን በቂልነቱ ከመገናኘት፣

ግልገሎቿን የተነጠቀችን ድብ መጋፈጥ ይሻላል።

13በበጎ ፈንታ ክፉ የሚመልስ ሰው፣

ክፉ ነገር ከቤቱ አይርቅም።

14ጠብ መጫር ግድብን እንደ መሸንቈር ነው፤

ስለዚህ ጠብ ከመጫሩ በፊት ከነገር ራቅ።

15በደለኛውን ንጹሕ ማድረግ ሆነ፣ ንጹሑን በደለኛ ማድረግ፣

ሁለቱም በእግዚአብሔር ዘንድ አስጸያፊ ናቸው።

16ጥበብን ለማግኘት ፍላጎት ስለሌለው፣

ተላላ እጅ የገባ ገንዘብ ጥቅሙ ምንድን ነው?

17ወዳጅ ምንጊዜም ወዳጅ ነው፤

ወንድምም ለክፉ ቀን ይወለዳል።

18ማስተዋል የጐደለው ሰው ቃል በመግባት እጅ ይመታል፤

ለወዳጁም ዋስ ይሆናል።

19ጠብ የሚወድድ ኀጢአትን ይወድዳል፤

በሩን ከፍ አድርጎ የሚሠራም ጥፋትን ይጋብዛል።

20ጠማማ ልብ ያለው ሰው አይሳካለትም፤

በአንደበቱ የሚቀላምድም መከራ ላይ ይወድቃል።

21ተላላ ልጅ መውለድ ሐዘን ያስከትላል፤

የተላላም አባት ደስታ የለውም።

22ደስተኛ ልብ ጥሩ መድኀኒት ነው፤

የተሰበረ መንፈስ ግን ዐጥንትን ያደርቃል።

23ክፉ ሰው ፍትሕ ለማዛባት፣

በስውር ጕቦ ይቀበላል።

24አስተዋይ ሰው ጥበብን ከፊቱ አይለያትም፤

የተላሎች ዐይኖች ግን እስከ ምድር ዳርቻ ይንከራተታሉ።

25ተላላ ልጅ በአባቱ ላይ ሐዘን ያስከትላል፤

ለወለደችውም ምሬት ይሆንባታል።

26ንጹሑን ሰው መቅጣት ተገቢ አይደለም፤

ሹሞችን ስለ ቅንነታቸው መግረፍ መልካም አይደለም።

27ዐዋቂ ሰው ንግግሩ ቍጥብ ነው፤

አስተዋይም መንፈሱ የረጋ ነው።

28አላዋቂ እንኳ ዝም ቢል ጠቢብ፣

አንደበቱንም ቢገዛ አስተዋይ ይመስላል።

New International Version – UK

Proverbs 17:1-28

1Better a dry crust with peace and quiet

than a house full of feasting, with strife.

2A prudent servant will rule over a disgraceful son

and will share the inheritance as one of the family.

3The crucible for silver and the furnace for gold,

but the Lord tests the heart.

4A wicked person listens to deceitful lips;

a liar pays attention to a destructive tongue.

5Whoever mocks the poor shows contempt for their Maker;

whoever gloats over disaster will not go unpunished.

6Children’s children are a crown to the aged,

and parents are the pride of their children.

7Eloquent lips are unsuited to a godless fool –

how much worse lying lips to a ruler!

8A bribe is seen as a charm by the one who gives it;

they think success will come at every turn.

9Whoever would foster love covers over an offence,

but whoever repeats the matter separates close friends.

10A rebuke impresses a discerning person

more than a hundred lashes a fool.

11Evildoers foster rebellion against God;

the messenger of death will be sent against them.

12Better to meet a bear robbed of her cubs

than a fool bent on folly.

13Evil will never leave the house

of one who pays back evil for good.

14Starting a quarrel is like breaching a dam;

so drop the matter before a dispute breaks out.

15Acquitting the guilty and condemning the innocent –

the Lord detests them both.

16Why should fools have money in hand to buy wisdom,

when they are not able to understand it?

17A friend loves at all times,

and a brother is born for a time of adversity.

18One who has no sense shakes hands in pledge

and puts up security for a neighbour.

19Whoever loves a quarrel loves sin;

whoever builds a high gate invites destruction.

20One whose heart is corrupt does not prosper;

one whose tongue is perverse falls into trouble.

21To have a fool for a child brings grief;

there is no joy for the parent of a godless fool.

22A cheerful heart is good medicine,

but a crushed spirit dries up the bones.

23The wicked accept bribes in secret

to pervert the course of justice.

24A discerning person keeps wisdom in view,

but a fool’s eyes wander to the ends of the earth.

25A foolish son brings grief to his father

and bitterness to the mother who bore him.

26If imposing a fine on the innocent is not good,

surely to flog honest officials is not right.

27The one who has knowledge uses words with restraint,

and whoever has understanding is even-tempered.

28Even fools are thought wise if they keep silent,

and discerning if they hold their tongues.