ምሳሌ 16 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 16:1-33

1የልብ ዕቅድ የሰው ነው፤

የአንደበት መልስ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

2ለሰው መንገዱ ሁሉ ንጹሕ መስሎ ይታየዋል፤

መነሻ ሐሳቡ ግን በእግዚአብሔር ይመዘናል።

3የምታደርገውን ሁሉ ለእግዚአብሔር ዐደራ ስጥ፤

ዕቅድህም ሁሉ ይሳካልሃል።

4እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር ለራሱ ዐላማ ሠርቷል፤

ክፉዎችንም እንኳ ለጥፋት ቀን አዘጋጅቷል።

5እግዚአብሔር በልብ የሚታበዩትን ሁሉ ይጸየፋል፤

እነርሱም ከቅጣት እንደማያመልጡ በርግጥ ዕወቅ።

6በፍቅርና በታማኝነት ኀጢአት ይሰረያል፤

እግዚአብሔርን በመፍራት ሰው ከክፋት ይርቃል።

7የሰው መንገድ እግዚአብሔርን ደስ ሲያሰኘው፣

ጠላቶቹ እንኳ አብረውት በሰላም እንዲኖሩ ያደርጋል።

8ከጽድቅ ጋር ጥቂቱ ነገር፣

በግፍ ከሚገኝ ብዙ ትርፍ ይሻላል።

9ሰው በልቡ መንገዱን ያቅዳል፤

እግዚአብሔር ግን ርምጃውን ይወስንለታል።

10የንጉሥ ከንፈሮች እንደ አምላክ ቃል ይናገራሉ፤

አንደበቱ ፍትሕን ያዛባ ዘንድ አይገባም።

11ሐቀኛ መስፈሪያና ሚዛን ከእግዚአብሔር ናቸው፤

በከረጢት ውስጥ ያሉት መመዘኛዎችም ሁሉ ሥራዎቹ ናቸው።

12ክፋትን ማድረግ ለነገሥታት አስጸያፊ ነው፤

ዙፋን የሚጸናው በጽድቅ ነውና።

13ነገሥታት በታማኝ ከንፈሮች ደስ ይላቸዋል፤

እውነት የሚናገረውን ሰው ይወድዱታል።

14የንጉሥ ቍጣ የሞት መልእክተኛ ነው፤

ጠቢብ ሰው ግን ቍጣውን ያበርዳል።

15የንጉሥ ፊት ሲፈካ ሕይወት አለ፤

በጎነቱም ዝናብ እንዳዘለ የበልግ ደመና ነው።

16ከወርቅ ይልቅ ጥበብን ማግኘት፣

ከብርም ማስተዋልን መምረጥ ምንኛ ይበልጣል!

17የቅኖች ጐዳና ከክፋት የራቀ ነው፤

መንገዱንም የሚጠብቅ ሕይወቱን ይጠብቃል።

18ትዕቢት ጥፋትን፣

የእብሪት መንፈስም ውድቀትን ትቀድማለች።

19በተዋረደ መንፈስ ከተጨቈኑት ጋር መሆን፣

ከትዕቢተኞች ጋር ብዝበዛን ከመካፈል ይሻላል።

20ምክርን የሚሰማ ይለመልማል፤

በእግዚአብሔርም የሚታመን ቡሩክ ነው።

21ልባቸው ጠቢብ የሆነ አስተዋዮች ይባላሉ፤

ደስ የሚያሰኙ ቃላትም ዕውቀትን ያዳብራሉ።16፥21 ወይም ቃላትም ተደማጭነት ያስገኛሉ

22ማስተዋልን ገንዘብ ላደረጋት የሕይወት ምንጭ ናት፤

ቂልነት ግን በተላሎች ላይ ቅጣት ታመጣባቸዋለች።

23የጠቢብ ሰው ልብ አንደበቱን ይመራል፤

ከንፈሮቹም ዕውቀትን ያዳብራሉ።16፥23 ወይም አንደበቱን አሳማኝ ያደርጋሉ

24ደስ የሚያሰኝ ቃል የማር ወለላ ነው፤

ለነፍስ ጣፋጭ፣ ለዐጥንትም ፈውስ ነው።

25ለሰው ቀና መስሎ የሚታይ መንገድ አለ፤

በመጨረሻ ግን ወደ ሞት ይመራል።

26ሠራተኛን የዕለት ጕርስ ፍላጎቱ ታታሪ ያደርገዋል፤

ራቡም ይገፋፋዋል።

27ወራዳ ሰው ክፋትን ያውጠነጥናል፤

ንግግሩም እንደሚለበልብ እሳት ነው።

28ጠማማ ሰው ጠብን ይዘራል፤

ሐሜተኛም የቅርብ ወዳጆችን ይለያያል።

29ክፉ ሰው ባልንጀራውን ያባብለዋል፤

መልካም ወዳልሆነውም መንገድ ይመራዋል።

30በዐይኑ የሚጠቅስ ሰው ጠማማነትን ያውጠነጥናል፤

በከንፈሩ የሚያሽሟጥጥም ወደ ክፋት ያዘነብላል።

31ሽበት የክብር ዘውድ ነው፤

የሚገኘውም በጽድቅ ሕይወት ነው።

32ታጋሽ ሰው ከጦረኛ፣

ስሜቱን የሚገዛም ከተማን በጕልበቱ ከሚይዝ ይበልጣል።

33ዕጣ በጕያ ውስጥ ይጣላል፤

ውሳኔው በሙሉ ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

Ketab El Hayat

الأمثال 16:1-33

1يَسْعَى الإِنْسَانُ بِالتَّفْكِيرِ وَالتَّدْبِيرِ، إِنَّمَا الرَّبُّ يُعْطِي الْجَوَابَ الْفَاصِلَ. 2جَمِيعُ تَصَرُّفَاتِ الإِنْسَانِ تَبْدُو نَقِيَّةً فِي عَيْنَيْ نَفْسِهِ، وَلَكِنَّ الرَّبَّ مُطَّلِعٌ عَلَى حَوَافِزِ الأَرْوَاحِ. 3اطْرَحْ عَلَى الرَّبِّ أَعْمَالَكَ فَتَثْبُتَ مَقَاصِدُكَ. 4لِكُلِّ شَيْءٍ صَنَعَهُ الرَّبُّ غَرَضٌ فِي ذَاتِهِ، حَتَّى الشِّرِّيرِ لِيَوْمِ الضِّيقِ. 5كُلُّ مُتَكَبِّرِ الْقَلْبِ رِجْسٌ عِنْدَ الرَّبِّ، وَلَنْ يُفْلِتَ حَتْماً مِنَ الْعِقَابِ. 6بِالرَّحْمَةِ وَالْحَقِّ يُسْتَرُ الإِثْمُ، وَبِتَقْوَى الرَّبِّ يَتَفَادَى الإِنْسَانُ الْوُقُوعَ فِي الشَّرِّ. 7إِذَا رَضِيَ الرَّبُّ عَنْ تَصَرُّفَاتِ الإِنْسَانِ، جَعَلَ أَعْدَاءَهُ أَيْضاً يُسَالِمُونَهُ. 8الْمَالُ الْقَلِيلُ مَعَ الْعَدْلِ خَيْرٌ مِنْ دَخْلٍ وَفِيرٍ حَرَامٍ. 9عَقْلُ الإِنْسَانِ يَسْعَى فِي تَخْطِيطِ طَرِيقِهِ، وَالرَّبُّ يُوَجِّهُ خَطْوَاتِهِ. 10تَنْطِقُ شَفَتَا الْمَلِكِ بِالْوَحْيِ، وَفَمُهُ لَا يَخُونُ فِي الْقَضَاءِ.

11لِلرَّبِّ مِيزَانُ الْعَدْلِ وَقِسْطَاسُهُ، وَجَمِيعُ مَعَايِيرِ كِيسِ التَّاجِرِ مِنْ صُنْعِهِ.

12مِنَ الرِّجْسِ أَنْ يَرْتَكِبَ الْمَلِكُ الشَّرَّ، لأَنَّ الْعَرْشَ يَقُومُ عَلَى الْبِرِّ. 13الشِّفَاهُ النَّاطِقَةُ بِالْعَدْلِ مَسَرَّةُ الْمُلُوكِ، وَهُمْ يُحِبُّونَ الْمُتَكَلِّمَ بِالْحَقِّ. 14غَضَبُ الْمَلِكِ رَسُولُ الْمَوْتِ، وَعَلَى الْحَكِيمِ اسْتِرْضَاؤُهُ. 15فِي بَشَاشَةِ وَجْهِ الْمَلِكِ حَيَاةٌ، وَرِضَاهُ كَسَحَابِ الْمَطَرِ الْمُتَأَخِّرِ. 16اقْتِنَاءُ الْحِكْمَةِ أَفْضَلُ مِنَ الذَّهَبِ، وَإِحْرَازُ الْفِطْنَةِ خَيْرٌ مِنَ الْفِضَّةِ. 17مَنْهَجُ الْمُسْتَقِيمِينَ تَفَادِيهِمْ سَبِيلَ الشَّرِّ، وَمَنْ يَصُونُ مَسْلَكَهُ يَصُونُ نَفْسَهُ.

18قَبْلَ الانْكِسَارِ الْكِبْرِيَاءُ، وَقَبْلَ السُّقُوطِ غَطْرَسَةُ الرُّوحِ. 19اتِّضَاعُ الرُّوحِ مَعَ الْوُدَعَاءِ خَيْرٌ مِنِ اقْتِسَامِ الْغَنِيمَةِ مَعَ الْمُتَكَبِّرِينَ. 20مَنْ يَتَعَقَّلُ بِكَلِمَةِ اللهِ يُحَالِفُهُ التَّوْفِيقُ، وَطُوبَى لِمَنْ يَتَّكِلُ عَلَى الرَّبِّ. 21الْحَكِيمُ الْقَلْبِ يُدْعَى فَهِيماً، وَعُذُوبَةُ الْمَنْطِقِ تَزِيدُ مِنْ قُوَّةِ الإِقْنَاعِ. 22الْفِطْنَةُ يَنْبُوعُ حَيَاةٍ لِصَاحِبِهَا، وَعِقَابُ الْجَاهِلِ فِي حَمَاقَتِهِ. 23عَقْلُ الْحَكِيمِ يُرْشِدُ فَمَهُ، وَيَزِيدُ مَنْطِقَهُ قُوَّةَ إِقْنَاعٍ. 24عُذُوبَةُ الْكَلامِ شَهْدُ عَسَلٍ، حُلْوةٌ لِلنَّفْسِ وَعَافِيَةٌ لِلْجَسَدِ.

25رُبَّ طَرِيقٍ تَبْدُو لِلإِنْسَانِ قَوِيمَةً وَلَكِنَّ عَاقِبَتَهَا تُفْضِي إِلَى دُرُوبِ الْمَوْتِ. 26شَهِيَّةُ الْعَامِلِ حَافِزُ عَمَلِهِ، لأَنَّ فَمَهُ الْجَائِعَ يَحُثُّهُ عَلَيْهِ. 27الرَّجُلُ اللَّئِيمُ يَنْبِشُ الشَّرَّ، وَعَلَى شَفَتَيْهِ تَتَوَهَّجُ نَارٌ مُتَّقِدَةٌ. 28الْمُنَافِقُ يُثِيرُ الْخُصُومَاتِ، وَالنَّمَّامُ يُفَرِّقُ الأَصْدِقَاءَ. 29الرَّجُلُ الظَّالِمُ يَسْتَغْوِي قَرِيبَهُ، وَيَجْعَلُهُ يَتَنَكَّبُ عَنْ سَوَاءِ السَّبِيلِ. 30مَنْ يَغْمِزُ بِعَيْنَيْهِ هُوَ مُتَآمِرٌ بِالْمَكَائِدِ، وَمَنْ يَعُضُّ عَلَى شَفَتَيْهِ فَقَدْ أَتَمَّ خُطَّةَ الشَّرِّ. 31الشَّيْبَةُ إِكْلِيلُ بَهَاءٍ، وَلاسِيَّمَا فِي طَرِيقِ الْبِرِّ. 32الْبَطِيءُ الْغَضَبِ خَيْرٌ مِنَ الْمُحَارِبِ الْعَاتِي، وَالضَّابِطُ أَهْوَاءَ رُوحِهِ خَيْرٌ مِنْ قَاهِرِ الْمُدُنِ. 33تُلْقَى الْقُرْعَةُ فِي الْحِضْنِ، وَلَكِنَّ الْقَرَارَ مَرْهُونٌ كُلُّهُ لأَمْرِ الرَّبِّ.