ምሳሌ 14 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 14:1-35

1ጠቢብ ሴት ቤቷን ትሠራለች፤

ተላላ ሴት ግን በገዛ እጇ ታፈርሰዋለች።

2አካሄዱ ቅን የሆነ ሰው እግዚአብሔርን ይፈራል፤

መንገዱ ጠማማ የሆነ ግን ይንቀዋል።

3የተላላ ሰው ንግግር ለጀርባው በትር ታስከትልበታለች፤

የጥበበኛ ከንፈር ግን ትጠብቃቸዋለች።

4በሬዎች በሌሉበት ገንዳው ባዶ ይሆናል፤

በበሬ ጕልበት ግን ብዙ ምርት ይገኛል።

5ታማኝ ምስክር አይዋሽም፤

ሐሰተኛ ምስክር ግን ውሸትን ይዘከዝካል።

6ፌዘኛ ጥበብን ይሻል፤ ሆኖም አያገኛትም፤

ዕውቀት ግን ለአስተዋዮች በቀላሉ ትገኛለች።

7ከተላላ ሰው ራቅ፣

ከከንፈሮቹ ዕውቀት አታገኝምና።

8የአስተዋዮች ጥበብ መንገዳቸውን ልብ ማለት ነው፤

የተላሎች ሞኝነት ግን መታለል ነው።

9ተላሎች በሚያቀርቡት የበደል ካሳ ያፌዛሉ፤

በቅኖች መካከል ግን በጎ ፈቃድ ትገኛለች።

10እያንዳንዱ ልብ የራሱን መራራ ሐዘን ያውቃል፤

ደስታውንም ማንም ሊጋራው አይችልም።

11የክፉዎች ቤት ይፈርሳል፤

የቅኖች ድንኳን ግን ይስፋፋል።

12ለሰው ቀና መስሎ የሚታይ መንገድ አለ፤

በመጨረሻ ግን ወደ ሞት ያደርሳል።

13በሣቅ ጊዜ እንኳ ልብ ይተክዛል፤

ደስታም በሐዘን ሊፈጸም ይችላል።

14ልባቸውን ከጽድቅ የሚመልሱ የእጃቸውን ሙሉ ዋጋ ይቀበላሉ፤

ደግ ሰውም ወሮታውን ያገኛል።

15ተላላ ሰው ሁሉን ያምናል፤

አስተዋይ ግን ርምጃውን ያስተውላል።

16ጠቢብ ሰው ጥንቁቅ ነው፤ ከክፉም ይርቃል፤

ተላላ ግን ችኵልና ደንታ ቢስ ነው።

17ግልፍተኛ ሰው የቂል ተግባር ይፈጽማል፤

መሠሪም ሰው አይወደድም።

18ብስለት የሌላቸው ተላላነትን ይወርሳሉ፤

አስተዋዮች ግን ዕውቀትን እንደ ዘውድ ይጭናሉ።

19ክፉዎች በደጎች ፊት፣

ኀጥኣንም በጻድቃን ደጅ ያጐነብሳሉ።

20ድኾችን ወዳጆቻቸው እንኳ ይጠሏቸዋል፤

ባለጠጎች ግን ብዙ ወዳጆች አሏቸው።

21ጎረቤቱን የሚንቅ ኀጢአት ይሠራል፤

ለተቸገሩት የሚራራ ግን ቡሩክ ነው።

22ክፉ ነገር የሚያቅዱ ከትክክለኛው መንገድ ይወጡ የለምን?

በጎ ነገር የሚያቅዱ ግን ፍቅርንና ታማኝነትን ያተርፋሉ።14፥22 ወይም ታማኝነትን ያሳያሉ

23ለፍተው የሠሩት ሁሉ ትርፍ ያስገኛል፤

ከንቱ ወሬ ግን ወደ ድኽነት ያመራል።

24ጠቢባን ብልጽግና ዘውዳቸው ነው፤

የተላሎች ተላላነት ግን ፍሬው ከንቱነት ነው።

25እውነተኛ ምስክር ሕይወት ያድናል፤

ሐሰተኛ ምስክር ግን አባይ ነው።

26እግዚአብሔርን የሚፈራ ጽኑ ዐምባ አለው፤

ልጆቹም መጠጊያ ይኖራቸዋል።

27እግዚአብሔርን መፍራት የሕይወት ምንጭ ነው፤

ሰውን ከሞት ወጥመድ ያድነዋል።

28የሕዝብ ብዛት የንጉሥ ክብር ሲሆን፣

የዜጎች ማነስ ግን ለገዥ መጥፊያው ነው።

29ታጋሽ ሰው ትልቅ ማስተዋል አለው፤

ግልፍተኛ ሰው ግን ቂልነትን ይገልጣል።

30ሰላም ያለው ልብ ለሰውነት ሕይወት ይሰጣል፤

ቅናት ግን ዐጥንትን ያነቅዛል።

31ድኾችን የሚያስጨንቅ ፈጣሪያቸውን ይንቃል፤

ለተቸገሩ የሚራራ ሁሉ ግን አምላክን ያከብራል።

32ክፉዎች በክፋታቸው ይወድቃሉ፤

ጻድቃን ግን በሞት ጊዜ እንኳ መጠጊያ አላቸው።

33ጥበብ በአስተዋዮች ልብ ታድራለች፤

በተላሎች መካከል ራሷን ትገልጣለች።14፥33 ዕብራይስጡ፣ የሰብዓ ሊቃናትና የሱርሰት ትርጕሞች በተላሎች ልብ ግን አትታወቅም ይላሉ።

34ጽድቅ ሕዝብን ከፍ ከፍ ታደርጋለች፤

ኀጢአት ግን ለየትኛውም ሕዝብ ውርደት ነው።

35ጠቢብ አገልጋይ ንጉሥን ደስ ያሰኛል፤

አሳፋሪ አገልጋይ ግን ቍጣውን በራሱ ላይ ያመጣል።

New International Version

Proverbs 14:1-35

1The wise woman builds her house,

but with her own hands the foolish one tears hers down.

2Whoever fears the Lord walks uprightly,

but those who despise him are devious in their ways.

3A fool’s mouth lashes out with pride,

but the lips of the wise protect them.

4Where there are no oxen, the manger is empty,

but from the strength of an ox come abundant harvests.

5An honest witness does not deceive,

but a false witness pours out lies.

6The mocker seeks wisdom and finds none,

but knowledge comes easily to the discerning.

7Stay away from a fool,

for you will not find knowledge on their lips.

8The wisdom of the prudent is to give thought to their ways,

but the folly of fools is deception.

9Fools mock at making amends for sin,

but goodwill is found among the upright.

10Each heart knows its own bitterness,

and no one else can share its joy.

11The house of the wicked will be destroyed,

but the tent of the upright will flourish.

12There is a way that appears to be right,

but in the end it leads to death.

13Even in laughter the heart may ache,

and rejoicing may end in grief.

14The faithless will be fully repaid for their ways,

and the good rewarded for theirs.

15The simple believe anything,

but the prudent give thought to their steps.

16The wise fear the Lord and shun evil,

but a fool is hotheaded and yet feels secure.

17A quick-tempered person does foolish things,

and the one who devises evil schemes is hated.

18The simple inherit folly,

but the prudent are crowned with knowledge.

19Evildoers will bow down in the presence of the good,

and the wicked at the gates of the righteous.

20The poor are shunned even by their neighbors,

but the rich have many friends.

21It is a sin to despise one’s neighbor,

but blessed is the one who is kind to the needy.

22Do not those who plot evil go astray?

But those who plan what is good find14:22 Or show love and faithfulness.

23All hard work brings a profit,

but mere talk leads only to poverty.

24The wealth of the wise is their crown,

but the folly of fools yields folly.

25A truthful witness saves lives,

but a false witness is deceitful.

26Whoever fears the Lord has a secure fortress,

and for their children it will be a refuge.

27The fear of the Lord is a fountain of life,

turning a person from the snares of death.

28A large population is a king’s glory,

but without subjects a prince is ruined.

29Whoever is patient has great understanding,

but one who is quick-tempered displays folly.

30A heart at peace gives life to the body,

but envy rots the bones.

31Whoever oppresses the poor shows contempt for their Maker,

but whoever is kind to the needy honors God.

32When calamity comes, the wicked are brought down,

but even in death the righteous seek refuge in God.

33Wisdom reposes in the heart of the discerning

and even among fools she lets herself be known.14:33 Hebrew; Septuagint and Syriac discerning / but in the heart of fools she is not known

34Righteousness exalts a nation,

but sin condemns any people.

35A king delights in a wise servant,

but a shameful servant arouses his fury.