ማቴዎስ 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 4:1-25

የኢየሱስ መፈተን

4፥1-11 ተጓ ምብ – ማር 1፥1213ሉቃ 4፥1-13

1ከዚህ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን በዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው። 2አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከጾመ በኋላ ተራበ። 3ፈታኙም ወደ ኢየሱስ ቀርቦ፣ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ እነዚህን ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ እዘዝ” አለው።

4ኢየሱስም፣ “ ‘ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣው ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም’ ተብሎ ተጽፏል” ሲል መለሰለት።

5ቀጥሎም ዲያብሎስ ኢየሱስን ወደ ቅድስት ከተማ በመውሰድ ከቤተ መቅደሱም ዐናት ላይ አውጥቶ፣ 6“የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ ራስህን ወደ መሬት ወርውር፤ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና፤

“ ‘እግርህ በድንጋይ እንዳይሰናከል፣

በእጃቸው ያነሡህ ዘንድ፣

መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዝልሃል።’ ”

7ኢየሱስም፣ “እንደዚሁም በመጻሕፍት፣ ‘እግዚአብሔር አምላክህን አትፈታተነው’ ተብሎ ተጽፏል” በማለት መለሰለት።

8እንደ ገናም ዲያብሎስ ኢየሱስን እጅግ ከፍ ወዳለ ተራራ አወጣው፤ የዓለምንም መንግሥታት ከነክብራቸው አሳየውና፣ 9“ወድቀህ ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ” አለው።

10ኢየሱስም፣ “አንተ ሰይጣን ከፊቴ ራቅ! ‘ለአምላክህ ለእግዚአብሔር ስገድ፤ እርሱንም ብቻ አምልክ’ ተብሎ ተጽፏልና” አለው።

11ከዚያም ዲያብሎስ ትቶት ሄደ፤ መላእክትም መጥተው አገለገሉት።

ኢየሱስ ስብከት መጀመሩ

12ኢየሱስ የዮሐንስን መታሰር በሰማ ጊዜ ወደ ገሊላ ተመለሰ። 13የናዝሬትንም ከተማ ትቶ፣ በዛብሎንና በንፍታሌም አካባቢ በባሕሩ አጠገብ በምትገኘው በቅፍርናሆም ከተማ መኖር ጀመረ። 14በዚህም በነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ተብሎ የተነገረው ትንቢት ተፈጸመ፤

15“የዛብሎን ምድር፣ የንፍታሌም ምድር፣

ከዮርዳኖስ ማዶ በባሕር መንገድ አጠገብ፣

ያለው የአሕዛብ ገሊላ፣

16በጨለማ የሚኖር ሕዝብ፣

ታላቅ ብርሃን አየ፤

በሞት ጥላ ምድር ላለው፣

ብርሃን ወጣለት።”

17ከዚያ ጊዜ አንሥቶ ኢየሱስ፣ “ንስሓ ግቡ፤ መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና” እያለ መስበክ ጀመረ።

የመጀመሪያዎቹ ደቀ መዛሙርት መጠራት

4፥18-22 ተጓ ምብ – ማር 1፥16-20ሉቃ 5፥2-11ዮሐ 1፥35-42

18ኢየሱስ በገሊላ ባሕር አጠገብ ሲያልፍ፣ ሁለት ወንድማማቾች ማለትም፣ ጴጥሮስ የተባለውን ስምዖንንና ወንድሙን እንድርያስን አያቸው። ዓሣ አጥማጆች ነበሩና መረባቸውን ወደ ባሕሩ ይጥሉ ነበር። 19ኢየሱስም፣ “ኑ፣ ተከተሉኝ፤ ሰዎችን አጥማጆች አደርጋችኋለሁ” አላቸው። 20ወዲያው መረባቸውን ትተው ተከተሉት።

21ዐለፍ እንዳለም፣ ሌሎች ሁለት ወንድማማቾች፣ የዘብዴዎስን ልጅ ያዕቆብንና ወንድሙን ዮሐንስን አየ። ከአባታቸው ከዘብዴዎስ ጋር በጀልባ ውስጥ መረባቸውን ያበጁ ነበር። ኢየሱስም ጠራቸው፤ 22ወዲያውኑ ጀልባቸውንም ሆነ አባታቸውን ትተው ተከተሉት።

የበሽተኞች መፈወስ

23ኢየሱስም በምኵራቦቻቸው እያስተማረ፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት የምሥራች ቃል እየሰበከ፣ በሕዝቡ መካከል ማንኛውንም ደዌና ሕመም እየፈወሰ በመላው ገሊላ ይዘዋወር ነበር። 24ከዚህም የተነሣ ዝናው በመላዋ ሶርያ ተሰማ፤ ሕዝቡም በተለያዩ በሽታዎች የታመሙትን፣ በክፉ ደዌ የሚሠቃዩትን፣ አጋንንት ያደሩባቸውን፣ የሚጥል በሽታ ያለባቸውን፣ ሽባዎችን ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ፤ ፈወሳቸውም። 25ከዚህም የተነሣ ከገሊላ፣ ከ “ዐሥሩ ከተሞች”፣ ከኢየሩሳሌም፣ ከይሁዳና ከዮርዳኖስ ማዶ የመጡ ብዙ ሰዎች ተከተሉት።

Thai New Contemporary Bible

มัทธิว 4:1-25

พระเยซูถูกมารทดลอง

(มก.1:12,13; ลก.4:1-13)

1จากนั้นพระวิญญาณทรงนำพระเยซูไปยังถิ่นกันดารเพื่อให้มารทดลอง 2หลังจากอดอาหารสี่สิบวันสี่สิบคืนแล้ว พระเยซูทรงหิว 3มารผู้ทดลองได้มาหาพระองค์และทูลว่า “ถ้าท่านเป็นพระบุตรของพระเจ้า จงสั่งก้อนหินเหล่านี้ให้กลายเป็นขนมปัง”

4พระเยซูตรัสตอบว่า “มีคำเขียนไว้ว่า ‘มนุษย์ไม่อาจดำรงชีวิตด้วยอาหารเพียงอย่างเดียวแต่ดำรงชีวิตด้วยทุกถ้อยคำจากพระโอษฐ์ของพระเจ้า’4:4 ฉธบ.8:3

5แล้วมารนำพระองค์ไปยังนครบริสุทธิ์และให้พระองค์ประทับยืนที่จุดสูงสุดของพระวิหาร 6แล้วทูลว่า “ถ้าท่านเป็นพระบุตรของพระเจ้าจงกระโดดลงไปเถิด เพราะมีคำเขียนไว้ว่า

“ ‘พระองค์จะทรงบัญชาทูตสวรรค์ของพระองค์ให้ดูแลท่าน

ทูตเหล่านั้นจะยื่นมือประคองท่าน

เพื่อไม่ให้เท้าของท่านกระทบหิน’4:6 สดด.91:11,12

7พระเยซูตรัสตอบเขาว่า “มีคำเขียนไว้เช่นกันว่า ‘อย่าทดลององค์พระผู้เป็นเจ้าพระเจ้าของท่าน’4:7 ฉธบ.6:16

8อีกครั้งหนึ่งมารนำพระองค์มายังภูเขาที่สูงมาก แล้วแสดงอาณาจักรทั้งปวงของโลกกับความโอ่อ่าตระการของอาณาจักรเหล่านั้นให้พระองค์ทอดพระเนตร 9แล้วทูลว่า “ทั้งหมดนี้เราจะยกให้ท่านหากท่านกราบนมัสการเรา”

10พระเยซูตรัสว่า “เจ้าซาตาน จงไปให้พ้น! เพราะมีคำเขียนไว้ว่า ‘จงนมัสการองค์พระผู้เป็นเจ้าพระเจ้าของท่านและปรนนิบัติพระองค์แต่ผู้เดียว’4:10 ฉธบ.6:13

11แล้วมารก็ละพระองค์ไปและเหล่าทูตสวรรค์มาปรนนิบัติพระองค์

พระเยซูทรงเริ่มเทศนา

12เมื่อพระเยซูทรงทราบว่ายอห์นถูกจับขังคุก พระองค์จึงเสด็จกลับไปยังแคว้นกาลิลี 13ทรงย้ายจากเมืองนาซาเร็ธมาประทับที่เมืองคาเปอรนาอุมซึ่งตั้งอยู่ริมทะเลสาบบริเวณเขตแดนเศบูลุนและนัฟทาลี 14เพื่อให้เป็นไปตามที่กล่าวไว้ผ่านทางผู้เผยพระวจนะอิสยาห์ว่า

15“ดินแดนเศบูลุนกับดินแดนนัฟทาลี

เส้นทางสู่ทะเลเลียบแม่น้ำจอร์แดน

กาลิลีแห่งชนต่างชาติ

16ประชากรผู้อยู่ในความมืด

ได้เห็นแสงสว่างยิ่งใหญ่

บรรดาผู้อาศัยในดินแดนแห่งเงาของความตาย

แสงสว่างเริ่มสาดต้องพวกเขาแล้ว”4:16 อสย.9:1,2

17ตั้งแต่นั้นมาพระเยซูทรงเริ่มต้นเทศนาว่า “จงกลับใจใหม่เพราะอาณาจักรสวรรค์มาใกล้แล้ว”

ทรงเรียกสาวกกลุ่มแรก

(มก.1:16-20; ลก.5:2-11; ยน.1:35-42)

18ขณะพระเยซูทรงดำเนินอยู่ริมทะเลกาลิลี ทรงเห็นชาวประมงสองพี่น้องคือซีโมนที่เรียกกันว่าเปโตรกับอันดรูว์น้องชายของเขากำลังทอดแหอยู่ที่ทะเลสาบ 19พระเยซูตรัสว่า “จงตามเรามาเถิด และเราจะตั้งท่านให้เป็นผู้หาคนดั่งหาปลา” 20ทั้งสองก็ละแหแล้วติดตามพระองค์ไปทันที

21เมื่อเสด็จต่อไปทรงพบพี่น้องอีกสองคน คือยากอบบุตรเศเบดีกับยอห์นน้องชายของเขากำลังชุนอวนอยู่ในเรือร่วมกับเศเบดีบิดาของพวกเขา พระเยซูทรงเรียกพวกเขา 22ทั้งสองก็ละเรือและบิดา แล้วติดตามพระองค์ไปทันที

พระเยซูทรงรักษาคนเจ็บป่วย

23พระเยซูเสด็จไปทั่วแคว้นกาลิลี ทรงสั่งสอนในธรรมศาลาของพวกเขา ประกาศข่าวประเสริฐเรื่องอาณาจักรของพระเจ้า และทรงรักษาโรคภัยไข้เจ็บทั้งปวงในหมู่ประชาชน 24กิตติศัพท์ของพระองค์เลื่องลือไปทั่วแคว้นซีเรีย และประชาชนนำคนเจ็บป่วยด้วยโรคต่างๆ มาให้พระเยซูทรงรักษา มีทั้งคนที่เจ็บปวดทรมาน คนถูกผีสิง คนเป็นโรคลมชัก คนเป็นอัมพาต และพระองค์ทรงรักษาพวกเขาให้หาย 25คนเป็นอันมากจากแคว้นกาลิลี แคว้นเดคาโปลิส4:25 คือทศบุรี กรุงเยรูซาเล็ม แคว้นยูเดียและจากอีกฟากหนึ่งของแม่น้ำจอร์แดนก็ติดตามพระองค์ไป