ማቴዎስ 4 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 4:1-25

የኢየሱስ መፈተን

4፥1-11 ተጓ ምብ – ማር 1፥1213ሉቃ 4፥1-13

1ከዚህ በኋላ መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን በዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው። 2አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከጾመ በኋላ ተራበ። 3ፈታኙም ወደ ኢየሱስ ቀርቦ፣ “የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ እነዚህን ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ እዘዝ” አለው።

4ኢየሱስም፣ “ ‘ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣው ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም’ ተብሎ ተጽፏል” ሲል መለሰለት።

5ቀጥሎም ዲያብሎስ ኢየሱስን ወደ ቅድስት ከተማ በመውሰድ ከቤተ መቅደሱም ዐናት ላይ አውጥቶ፣ 6“የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ ራስህን ወደ መሬት ወርውር፤ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና፤

“ ‘እግርህ በድንጋይ እንዳይሰናከል፣

በእጃቸው ያነሡህ ዘንድ፣

መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዝልሃል።’ ”

7ኢየሱስም፣ “እንደዚሁም በመጻሕፍት፣ ‘እግዚአብሔር አምላክህን አትፈታተነው’ ተብሎ ተጽፏል” በማለት መለሰለት።

8እንደ ገናም ዲያብሎስ ኢየሱስን እጅግ ከፍ ወዳለ ተራራ አወጣው፤ የዓለምንም መንግሥታት ከነክብራቸው አሳየውና፣ 9“ወድቀህ ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ” አለው።

10ኢየሱስም፣ “አንተ ሰይጣን ከፊቴ ራቅ! ‘ለአምላክህ ለእግዚአብሔር ስገድ፤ እርሱንም ብቻ አምልክ’ ተብሎ ተጽፏልና” አለው።

11ከዚያም ዲያብሎስ ትቶት ሄደ፤ መላእክትም መጥተው አገለገሉት።

ኢየሱስ ስብከት መጀመሩ

12ኢየሱስ የዮሐንስን መታሰር በሰማ ጊዜ ወደ ገሊላ ተመለሰ። 13የናዝሬትንም ከተማ ትቶ፣ በዛብሎንና በንፍታሌም አካባቢ በባሕሩ አጠገብ በምትገኘው በቅፍርናሆም ከተማ መኖር ጀመረ። 14በዚህም በነቢዩ ኢሳይያስ እንዲህ ተብሎ የተነገረው ትንቢት ተፈጸመ፤

15“የዛብሎን ምድር፣ የንፍታሌም ምድር፣

ከዮርዳኖስ ማዶ በባሕር መንገድ አጠገብ፣

ያለው የአሕዛብ ገሊላ፣

16በጨለማ የሚኖር ሕዝብ፣

ታላቅ ብርሃን አየ፤

በሞት ጥላ ምድር ላለው፣

ብርሃን ወጣለት።”

17ከዚያ ጊዜ አንሥቶ ኢየሱስ፣ “ንስሓ ግቡ፤ መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና” እያለ መስበክ ጀመረ።

የመጀመሪያዎቹ ደቀ መዛሙርት መጠራት

4፥18-22 ተጓ ምብ – ማር 1፥16-20ሉቃ 5፥2-11ዮሐ 1፥35-42

18ኢየሱስ በገሊላ ባሕር አጠገብ ሲያልፍ፣ ሁለት ወንድማማቾች ማለትም፣ ጴጥሮስ የተባለውን ስምዖንንና ወንድሙን እንድርያስን አያቸው። ዓሣ አጥማጆች ነበሩና መረባቸውን ወደ ባሕሩ ይጥሉ ነበር። 19ኢየሱስም፣ “ኑ፣ ተከተሉኝ፤ ሰዎችን አጥማጆች አደርጋችኋለሁ” አላቸው። 20ወዲያው መረባቸውን ትተው ተከተሉት።

21ዐለፍ እንዳለም፣ ሌሎች ሁለት ወንድማማቾች፣ የዘብዴዎስን ልጅ ያዕቆብንና ወንድሙን ዮሐንስን አየ። ከአባታቸው ከዘብዴዎስ ጋር በጀልባ ውስጥ መረባቸውን ያበጁ ነበር። ኢየሱስም ጠራቸው፤ 22ወዲያውኑ ጀልባቸውንም ሆነ አባታቸውን ትተው ተከተሉት።

የበሽተኞች መፈወስ

23ኢየሱስም በምኵራቦቻቸው እያስተማረ፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት የምሥራች ቃል እየሰበከ፣ በሕዝቡ መካከል ማንኛውንም ደዌና ሕመም እየፈወሰ በመላው ገሊላ ይዘዋወር ነበር። 24ከዚህም የተነሣ ዝናው በመላዋ ሶርያ ተሰማ፤ ሕዝቡም በተለያዩ በሽታዎች የታመሙትን፣ በክፉ ደዌ የሚሠቃዩትን፣ አጋንንት ያደሩባቸውን፣ የሚጥል በሽታ ያለባቸውን፣ ሽባዎችን ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ፤ ፈወሳቸውም። 25ከዚህም የተነሣ ከገሊላ፣ ከ “ዐሥሩ ከተሞች”፣ ከኢየሩሳሌም፣ ከይሁዳና ከዮርዳኖስ ማዶ የመጡ ብዙ ሰዎች ተከተሉት።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי מתי 4:1-25

1לאחר מכן, הרוח הובילה את ישוע אל המדבר כדי שהשטן ינסה אותו שם. 2במשך ארבעים יום וארבעים לילה ישוע לא אכל מאומה, ולבסוף היה רעב מאוד.

3”אם אתה באמת בן־אלוהים,“ אמר לו השטן, ”צווה על האבנים האלה להפוך לכיכרות לחם!“

4ישוע ענה לו: ”לא אצווה זאת, שהרי כתוב בתורה:4‏.4 ד 4 דברים ח 3 ’לא על הלחם לבדו יחיה האדם, כי על כל מוצא פי ה׳‘. “

5לאחר מכן הביא השטן את ישוע לירושלים, העלה אותו על גג בית־המקדש ואמר: 6”קפוץ למטה! הרי כתוב בתנ״ך:4‏.6 ד 6 תהלים צא 11‏-12 ’כי מלאכיו יצווה לך… ועל כפיים ישאונך, פן תיגוף באבן רגלך‘. “

7השיב לו ישוע: ”אבל כתוב גם:4‏.7 ד 7 דברים ו 16 ’לא תנסה את ה׳ אלוהיך‘. “

8לאחר מכן השטן העלה את ישוע על הר מאוד גבוה, הראה לו את כל המדינות המפוארות בעולם ואמר: 9”אם רק תכרע ברך ותשתחווה לי, אתן לך את כל אלה!“

10ישוע השיב: ”סור ממני, שטן! הרי כתוב: ’לה׳ אלוהיך תשתחווה ואותו לבדו תעבוד‘. “

11השטן הרפה ממנו, ומלאכים באו לשרת את ישוע.

12כאשר שמע ישוע על זה שיוחנן המטביל נאסר, הוא עזב את ארץ יהודה וחזר לביתו – לנצרת שבגליל. 13אחר כך ישוע עבר לגור בכפר־נחום שעל שפת הכינרת, באזור שבטי זבולון ונפתלי. 14כך התקיימה נבואת ישעיהו:4‏.14 ד 14 ישעיהו ח 23— ט 1

15”ארצה זבולון וארצה נפתלי,

דרך הים, עבר הירדן, גליל הגויים –

16העם ההלכים בחשך ראו אור גדול,

ישבי בארץ צלמוות – אור נָגַהּ עליהם!“

17מאותו יום והלאה ישוע התחיל להטיף: ”שובו בתשובה והאמינו בה׳, כי מלכות השמיים קרובה!“

18יום אחד כשישוע הלך על חוף הכינרת, הוא ראה שני אחים: שמעון (הנקרא גם פטרוס) ו‎אַנְדְּרֵי. השניים ישבו בסירה ודגו בעזרת רשת, כי היו דייגים במקצועם.

19”בואו אחרי!“ קרא להם ישוע. ”אני אעשה אתכם לדייגי אדם!“ 20שני האחים עזבו מיד את הרשתות שלהם והלכו אחריו.

21לא הרחק משם ראה ישוע עוד שני אחים, יעקב ויוחנן, יושבים בסירה עם אביהם זבדי, ומתקנים את רשתותיהם הקרועות. ישוע קרא גם להם, 22והשניים הפסיקו מיד את עבודתם, עזבו את אביהם והלכו אחריו.

23ישוע הסתובב בכל הגליל ולימד בבתי־הכנסת; בכל מקום בישר את החדשות הטובות על מלכות השמיים וריפא כל מיני מחלות. 24השמועות על הניסים שחולל פשטו מעבר לגבולות הגליל, וחולים באו אליו להירפא אפילו מסוריה. הובאו אליו אנשים אחוזי־שדים, מטורפים ומשותקים, וישוע ריפא את כולם. 25לכל מקום שהלך, הלכו אחריו המונים: מהגליל, מחו״ל, מירושלים, מיהודה ואף מעבר הירדן.