ማርቆስ 13 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 13:1-37

የመጨረሻው ዘመን ምልክቶች

13፥1-37 ተጓ ምብ – ማቴ 24፥1-51ሉቃ 21፥5-36

1ከቤተ መቅደስ ሲወጣ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ፣ “መምህር ሆይ፤ ድንጋዮቹ እንዴት እንደ ሆኑ፣ ሕንጻውም እንዴት ውብ እንደ ሆነ እይ” አለው።

2ኢየሱስም መልሶ፣ “እነዚህን ታላላቅ ሕንጻዎች ታያለህን? አንዱ ድንጋይ በሌላው ላይ እንደ ሆነ አይቀርም፤ ሁሉም ፈራሽ ነው” አለው።

3ኢየሱስ በቤተ መቅደሱ ትይዩ፣ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ተቀምጦ ሳለ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብ፣ ዮሐንስና እንድርያስ እንዲህ ሲሉ ጠየቁት፤ 4“ይህ መቼ እንደሚሆን ንገረን፤ የዚህስ ሁሉ ፍጻሜ ምልክቱ ምንድን ነው?”

5ኢየሱስም እንዲህ ይላቸው ጀመር፤ “ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ፤ 6ብዙዎች፣ ‘እኔ እርሱ ነኝ’ እያሉ በስሜ ይመጣሉ፤ ብዙዎችንም ያስታሉ። 7ስለ ጦርነትና ስለ ጦርነት ወሬ በምትሰሙበት ጊዜ አትደንግጡ፤ ይህማ መሆን አለበት፤ ፍጻሜው ግን ገና ነው። 8ሕዝብ በሕዝብ ላይ፣ መንግሥት በመንግሥት ላይ ይነሣል፤ በብዙ ቦታም የመሬት መንቀጥቀጥና ራብ ይሆናል፤ እነዚህ ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።

9“ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤ ለአካባቢ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጧችኋል፤ በምኵራብ ይገርፏችኋል፤ ምስክር ትሆኑም ዘንድ በእኔ ምክንያት በገዦችና በነገሥታት ፊት ትቆማላችሁ። 10አስቀድሞ ግን ወንጌል ለሕዝብ ሁሉ መሰበክ አለበት። 11ተይዛችሁ ለፍርድ በምትቀርቡበት ጊዜ፣ በዚያች ሰዓት የሚሰጣችሁን ተናገሩ እንጂ ምን እንናገራለን በማለት አስቀድማችሁ አትጨነቁ፤ የሚናገረው መንፈስ ቅዱስ እንጂ እናንተ አይደላችሁምና።

12“ወንድም ወንድሙን፣ አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፤ ልጆች በወላጆቻቸው ላይ ያምፃሉ፤ ይገድሏቸዋልም። 13በእኔ ምክንያት በሰው ሁሉ ዘንድ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻው የሚጸና ግን ይድናል።

14“ ‘የጥፋት ርኩሰት’ ስፍራው ባልሆነ ቦታ ቆሞ በምታዩት ጊዜ አንባቢው ያስተውል፤ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፤ 15በቤቱ ጣራ ላይ ያለ አይውረድ፤ ንብረቱንም ለማውጣት ወደ ቤቱ አይግባ፤ 16በዕርሻ ቦታ ያለ ልብሱን ለመውሰድ አይመለስ። 17በእነዚያ ቀናት ለነፍሰ ጡሮችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው! 18ይህም በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ፤ 19በመጀመሪያ እግዚአብሔር ፍጥረትን ከፈጠረበት ጊዜ አንሥቶ እስከ አሁን ድረስ፣ እንዲሁ ደግሞም ወደ ፊት አቻ የሌለው ታላቅ መከራ ይሆናልና። 20ጌታ ቀኖቹን ባያሳጥራቸው ኖሮ ማንም ባልዳነ ነበር፤ ስለ መረጣቸው ስለ ምርጦቹ ሲል ግን ቀኖቹን አሳጥሯል። 21በዚያን ጊዜ ማንም፣ ‘እነሆ፤ ክርስቶስ13፥21 ወይም መሲሑ እዚህ ነው?’ ቢላችሁ ወይም፣ ‘እነሆ፤ እዚያ ነው’ ቢላችሁ አትመኑ። 22ሐሰተኛ ክርስቶሶችና ሐሰተኛ ነቢያት ተነሥተው፣ ምልክቶችንና ድንቆችን በማድረግ፣ ቢቻላቸው የተመረጡትን እንኳ ያስታሉ። 23ስለዚህ ተጠንቀቁ፤ ጊዜው ሳይደርስ ሁሉን ነግሬአችኋለሁ።

24“በዚያን ጊዜ፣ ከመከራው በኋላ ‘ፀሓይ ትጨልማለች፣

“ ‘ጨረቃም ብርሃኗን አትሰጥም፤

25ከዋክብት ከሰማይ ይረግፋሉ፤

የሰማይ ኀይላትም ይናወጣሉ።’

26“በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በታላቅ ኀይልና ግርማ በደመና ሲመጣ ያዩታል። 27እርሱም መላእክቱን ልኮ ከአራቱ ነፋሳት፣ ከምድር ዳርቻ እስከ ሰማያት ዳርቻ ምርጦቹን ይሰበስባል።

28“ምሳሌውን ከበለስ ተማሩ፤ ቅርንጫፏ ሲለመልም፣ ቅጠሏ ሲያቈጠቍጥ በጋ እንደ ተቃረበ ታውቃላችሁ፤ 29እንዲሁ ደግሞ እነዚህ ነገሮች መፈጸማቸውን ስታዩ እንደ ቀረበ፣ በደጅም እንደ ሆነ ዕወቁ። 30እውነት እላችኋለሁ፣ እነዚህ ነገሮች እስከሚፈጸሙ ድረስ ይህ ትውልድ13፥30 ወይም ዘር አያልፍም፤ 31ሰማይና ምድር ያልፋሉ፣ ቃሌ ግን አያልፍም።

ቀኑና ሰዓቱ አይታወቅም

32“ነገር ግን ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያችም ሰዓት ከአብ በቀር፣ የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ፣ ወልድም ቢሆን፣ ማንም አያውቅም። 33ስለዚህ ጊዜው መቼ እንደሚሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፣ ጸልዩም13፥33 ጸልዩ የሚለው ቃል በአንዳንድ ቅጆች አይገኝም። 34ይህም ቤቱን ለአገልጋዮቹ ትቶ፣ እያንዳንዱን አገልጋይ በየሥራ ድርሻው ላይ አሰማርቶ፣ በረኛው ነቅቶ እንዲጠብቅ አዝዞ የሄደውን ሰው ይመስላል። 35እንግዲህ የቤቱ ባለቤት በምሽት ወይም በውድቅት፣ በዶሮ ጩኸት ወይም ጎሕ ሲቀድድ እንደሚመጣ አታውቁምና ተግታችሁ ጠብቁ፤ 36ድንገት ሲመጣ ተኝታችሁ እንዳያገኛችሁ፤ 37ለእናንተ የምነግራችሁን ለሰው ሁሉ እናገራለሁ፤ ተግታችሁ ጠብቁ!”

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי מרקוס 13:1-37

1כשיצא ישוע מבית־המקדש באותו יום, אחד מתלמידיו העיר: ”רבי, ראה אילו מבנים יפים ואיזו עבודת אבנים נפלאה!“

2”הבט היטב,“ ענה לו ישוע, ”כי כול הבנינים הגדולים האלה ייהרסו; אף אבן לא תישאר במקומה.“

3‏-4ישוע ישב על הר הזיתים, מול בית־המקדש, ופטרוס, יעקב ויוחנן ואַנְדְּרֵי שנשארו איתו שאלו: ”מתי יקרה הדבר? האם נקבל אזהרה מראש?“

5ישוע הסביר להם בהרחבה את העומד להתרחש: ”אל תתנו לאיש לרמות אתכם! 6אנשים רבים יבואו ויטענו: ’אני הוא המשיח‘, ויוליכו שולל אנשים רבים. 7במקומות שונים תפרוצנה מלחמות, אך אין זה עדיין הסוף.

8”מדינות וממלכות תילחמנה זו בזו, ובמקומות רבים יהיו רעידות אדמה ורעב. אלה יציינו רק את ראשית הצרות והסבל העתידים לבוא. 9אולם כשיתחילו דברים אלה להתרחש, היזהרו! כי צפויה לכם סכנה גדולה. אויביכם יגררו אתכם בכוח לבתי המשפט, יכו אתכם בבתי־הכנסת, ויאשימו אתכם לפני השלטונות על היותכם תלמידי. אולם זו תהיה לכם הזדמנות לספר להם על הבשורה. 10אך צריך שקודם הבשורה תוכרז לכל הגויים. 11כאשר יאסרו אתכם ויעמידו אתכם למשפט, אל תדאגו לעדותכם או להגנתכם מה להגיד, כי מה שיינתן לכם באותה שעה, את זה תגידו; כי לא אתם תדברו, אלא רוח הקודש ידבר בפיכם.

12”אח יבגוד באחיו ויסגירו למוות; אבות ימסרו את בניהם למוות; 13ילדים יקומו נגד הוריהם וייגרמו למותם. כולם ישנאו אתכם משום שאתם שייכים לי, אולם כל מי שיחזיק מעמד עד הסוף – ייוושע!

14”כאשר תראו את חילול הקודש בבית־המקדש שעליו דיבר דניאל, (הקורא – שים לב!) על כל תושבי יהודה לברוח להרים. 15‏-16אם אתה נמצא על גג ביתך – אל תיכנס הביתה; אם אתה בשדה – אל תחזור הביתה לקחת מעיל או כסף, כי אין זמן.

17”אוי לנשים ההרות ולמניקות באותם ימים! 18התפללו שכל זה לא יקרה בחורף, 19כי תקופה זאת תהיה איומה ונוראה; דבר כזה לא קרה מאז בריאת העולם, וגם לא יקרה אחר כך. 20אם האדון לא יקצר את הימים הנוראים האלה – איש לא יינצל. אבל הוא אכן יקצר את הסבל למען עמו הנבחר.

21”אם מישהו יאמר לכם באותם ימים: ’ראיתי את המשיח במקום פלוני!‘ או ’המשיח נמצא בכפר הסמוך!‘ אל תאמינו לו, 22כי משיחי־שקר ונביאי־שקר יקומו ויחוללו נסים ונפלאות אשר יתעו את האנשים, ואם יוכלו, הם יתעו אפילו את הנבחרים. 23ראו הוזהרתם!

24”לאחר הצרות של אותם ימים תחשך השמש, הירח ישחיר, 25הכוכבים יפלו מהשמים וכוחות השמים יתמוטטו.

26”ואז יראו אנשי הארץ את בן־האדם בא בעננים, בגבורה רבה ובכבוד. 27ואז הוא ישלח את מלאכיו, ויאסף את בחיריו מכל קצוות תבל. 28עץ התאנה ישמש לכם כדוגמה: כאשר הענפים מלבלבים והעלים ירוקים, אתם יודעים שהקיץ קרב. 29כאשר כל מה שסיפרתי לכם יתחיל להתרחש, דעו לכם שזה קרוב, שאני עומד בפתח.

30”אני אומר לכם: כל הדברים האלה יתרחשו לפני שיחלוף הדור הזה. 31השמים והארץ יחלפו, אבל דברי לא יחלפו.

32”איש אינו יודע את היום והשעה של התרחשויות אלה; המלאכים בשמים אינם יודעים זאת, ואפילו אני עצמי איני יודע את המועד המדויק. רק אבי שבשמים יודע זאת. 33עמדו על המשמר והיו מוכנים, מפני שאינכם יודעים מתי כל זה יתרחש.

34”משל דומה לזה הוא של אדם היוצא למסע בחו״ל. הוא משאיר עבודה לשכיריו לתקופת העדרו, ומצווה על השוער לעמוד על המשמר לקראת שובו בכל רגע. 35‏-37היו מוכנים! הלא אינכם יודעים מתי ישוב בעל הבית: בבוקר, בערב, מוקדם או מאוחר, פן יבוא וימצא אתכם ישנים. אני אומר שוב לכולכם: עמדו על המשמר!“