ሚክያስ 1 – NASV & NEN

New Amharic Standard Version

ሚክያስ 1:1-16

1በይሁዳ ነገሥታት በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን ወደ ሞሬታዊው ወደ ሚክያስ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል፣ ስለ ሰማርያና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ራእይ ይህ ነው፤

2እናንተ አሕዛብ ሆይ፤ ሁላችሁም ስሙ፤

ምድር ሆይ፤ በውስጧም የምትኖሩ ሁሉ አድምጡ፤

ጌታ ከቅዱስ መቅደሱ፣

ልዑል እግዚአብሔር በእናንተ ላይ ይመሰክርባችኋል።

በሰማርያና በኢየሩሳሌም ላይ የተላለፈ ፍርድ

3እነሆ፤ እግዚአብሔር ከመኖሪያ ስፍራው ይመጣል፤

ወርዶም በምድር ከፍታዎች ላይ ይራመዳል።

4ተራሮች ከሥሩ ይቀልጣሉ፤

ሸለቆዎችም ይሰነጠቃሉ፤

በእሳት ፊት እንዳለ ሰም፣

በገደል ላይ እንደሚወርድ ፈሳሽ ይሆናሉ።

5ይህ ሁሉ የሚሆነው ስለ ያዕቆብ በደል፣

ስለ እስራኤልም ቤት ኀጢአት ነው።

የያዕቆብ በደል ምንድን ነው?

ሰማርያ አይደለችምን?

የይሁዳስ የኰረብታ መስገጃ ምንድን ነው?

ኢየሩሳሌም አይደለችምን?

6“ስለዚህ ሰማርያን የፍርስራሽ ክምር፣

ወይን የሚተከልባትም ስፍራ አደርጋታለሁ፤

ድንጋዮቿን ወደ ሸለቆ አወርዳለሁ፤

መሠረቷንም ባዶ አደርጋለሁ።

7ጣዖቶቿ ሁሉ ይሰባበራሉ፤

ለቤተ መቅደሷ የቀረበው ገጸ በረከት በእሳት ይቃጠላል፤

ምስሎቿን ሁሉ እደመስሳለሁ፤

ገጸ በረከቷን በዝሙት ዐዳሪነት እንደ ሰበሰበች ሁሉ፣

አሁንም ገጸ በረከቷ የዝሙት ዐዳሪነት ዋጋ መቀበያ ይሆናል።”

ልቅሶና ሐዘን

8በዚህ ምክንያት አለቅሳለሁ፤ ዋይ ዋይም እላለሁ፤

ባዶ እግሬንና ዕርቃኔን እሄዳለሁ፤

እንደ ቀበሮ አላዝናለሁ፤

እንደ ጕጕትም አቃስታለሁ።

9ቍስሏ የማይሽር ነውና፤

ለይሁዳ ተርፏል፤

እስከ ሕዝቤ መግቢያ በር፣

እስከ ኢየሩሳሌም እንኳ ደርሷል።

10በጌት1፥10 ጌት የሚለው ቃል በዕብራይስጡ አውራ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። አታውሩት፤

ከቶም አታልቅሱ1፥10 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ሲስማማ፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን በአኮ ላይ አታልቅሱ ይላል። በአኮ የሚለው የዕብራይስጡ ቃል አለቀሰ ከሚለው የዕብራይስጡ ቃል ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው።

በቤትዓፍራ1፥10 ቤትዓፍራ ትርጕሙ የትቢያ ቤት ማለት ነው።

በትቢያ ላይ ተንከባለሉ።

11እናንት በሻፊር1፥11 ሻፊር ትርጕሙ አስደሳች ማለት ነው። የምትኖሩ፣

ዕርቃናችሁን ሆናችሁ በኀፍረት ዕለፉ፤

በጸዓናን1፥11 ጸዓናን የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ውጣ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የሚኖሩ

ከዚያ አይወጡም፤

ቤትዔጼል በሐዘን ላይ ናት፤

ለእናንተም መጠጊያ ልትሆን አትችልም።

12ከመከራው መገላገልን በመሻት፣

በማሮት1፥12 ማሮት የሚለው ቃል በዕብራይስጡ መራራ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የሚኖሩ በሥቃይ

ይወራጫሉ፤

እስከ ኢየሩሳሌም በር ሳይቀር፣

ክፉ ነገር ከእግዚአብሔር ዘንድ መጥቷልና።

13እናንት በለኪሶ1፥13 ለኪሶ የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ቡድን ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የምትኖሩ፣

ፈረሶችን ከሠረገላው ጋር አያይዙ፤

ለጽዮን ሴት ልጅ፣

የኀጢአት መጀመሪያ እናንት ነበራችሁ፤

የእስራኤል በደል

በእናንተ ዘንድ ተገኝቷልና።

14ስለዚህ እናንተ ለሞሬሼትጌት፣

ማጫ ትሰጣላችሁ፤

የአክዚብ1፥14 አክዚብ ትርጕሙ አታላይ ወይም ማታለል ማለት ነው። ከተማ፣

ለእስራኤል ነገሥታት መታለያ ትሆናለች።

15እናንት በመሪሳ1፥15 መሪሳ የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ድል አድራጊ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የምትኖሩ

ድል አድራጊ አመጣባችኋለሁ፤

ያ የእስራኤል ክብር የሆነው

ወደ ዓዶላም ይመጣል።

16ደስ ለምትሰኙባቸው ልጆቻችሁ፣

በሐዘን ራሳችሁን ተላጩ፤

ራሳችሁን እንደ አሞራ ራስ ተመለጡት፤

ከእናንተ በምርኮ ይወሰዳሉና።

Kiswahili Contemporary Version (Neno: Bibilia Takatifu)

Mika 1:1-16

11:1 Yer 26:18; 2Pet 1:21; 1Nya 3:12-13; Hos 1:1; Isa 1:1Neno la Bwana lilimjia Mika, Mmoreshethi, wakati wa utawala wa Yothamu, Ahazi na Hezekia, wafalme wa Yuda; ufunuo aliouona kuhusu Samaria na Yerusalemu.

21:2 Kum 4:26; 32:1; Yer 6:19; Mwa 31:50; Za 11:4; Isa 1:2Sikieni, enyi mataifa, enyi nyote,

sikilizeni, ee dunia na wote mliomo ndani yake,

ili Bwana Mwenyezi ashuhudie dhidi yenu,

Bwana kutoka Hekalu lake takatifu.

Hukumu Dhidi Ya Samaria Na Yerusalemu

31:3 Isa 18:4; 64:1; 26:21; Eze 3:12; Ebr 12:18, 19; Amo 4:13Tazama! Bwana anakuja kutoka mahali pake;

anashuka na kukanyaga

mahali palipoinuka juu pa dunia.

41:4 Za 46:2-6; Hes 16:31; Nah 1:5Milima inayeyuka chini yake

na mabonde yanagawanyika

kama nta mbele ya moto,

kama maji yatiririkayo kasi

kwenye mteremko.

51:5 Amo 8:14; Hos 5:5; Yer 2:18-19Yote haya ni kwa sababu ya kosa la Yakobo,

ni kwa sababu ya dhambi za nyumba ya Israeli.

Kosa la Yakobo ni lipi?

Je, sio Samaria?

Je, mahali pa juu pa Yuda pa kuabudia miungu ni nini?

Je, sio Yerusalemu?

61:6 Kum 20:6; Amo 5:11“Kwa hiyo nitaufanya Samaria kuwa lundo la kokoto,

mahali pa kuotesha mizabibu.

Nitayamwaga mawe yake katika bonde

na kuacha wazi misingi yake.

71:7 Eze 6:6; Kut 32:20; Kum 9:21; 23:17-18Sanamu zake zote

zitavunjwa vipande vipande;

zawadi zake zote za Hekalu

zitachomwa kwa moto;

nitaharibu vinyago vyake vyote.

Kwa kuwa alikusanya zawadi zake

kutokana na ujira wa kahaba,

nazo zitatumika tena

kulipa mishahara ya kahaba.”

Kulia Na Kuomboleza

81:8 Isa 15:3; 20:2Kwa ajili ya hili nitalia na kuomboleza;

nitatembea bila viatu na tena uchi.

Nitabweka kama mbweha

na kuomboleza kama bundi.

91:9 Yer 46:11; 10:19; 2Fal 18:13; Isa 3:26Kwa sababu jeraha lake halitibiki;

limekuja Yuda.

Limefika hasa kwenye lango la watu wangu,

hata Yerusalemu kwenyewe.

10Usiliseme hili huko Gathi;

usilie hata kidogo.

Huko Beth-le-Afra

gaagaa mavumbini.

111:11 Eze 23:29Piteni mkiwa uchi na wenye aibu,

ninyi mkaao Shafiri.

Wale waishio Saanani

hawatatoka nje.

Beth-Eseli iko katika maombolezo;

kinga yake imeondolewa kwako.

121:12 Yer 14:19; 40:2Wale waishio Marothi wanagaagaa kwa maumivu

wakingoja msaada,

kwa sababu maangamizi yamekuja

kutoka kwa Bwana,

hata katika lango la Yerusalemu.

131:13 Yos 10:3; Za 9:14Enyi mkaao Lakishi,

fungeni farasi kwenye magari ya vita.

Mlikuwa chanzo cha dhambi

kwa Binti Sayuni,

kwa kuwa makosa ya Israeli

yalikutwa kwako.

141:14 2Fal 16:8; Yos 15:44; Yer 15:18Kwa hiyo utaipa Moresheth-Gathi

zawadi za kuagana.

Mji wa Akzibu utaonyesha wazi udanganyifu

kwa wafalme wa Israeli.

151:15 Yos 15:44; 12:15Nitawaleteeni atakayewashinda

ninyi mnaoishi Maresha.

Yeye aliye utukufu wa Israeli

atakuja Adulamu.

161:16 Law 13:40; Ay 1:20; 2Fal 18:13; Amo 5:27; Kum 4:27Nyoeni nywele zenu katika kuomboleza

kwa ajili ya watoto wenu mnaowafurahia;

jifanyieni upara kama tai,

kwa kuwa watawaacha

na kwenda uhamishoni.