መዝሙር 94 – NASV & NSP

New Amharic Standard Version

መዝሙር 94:1-23

መዝሙር 94

የእግዚአብሔር ፍትሕ

1የበቀል አምላክ፣ አንተ እግዚአብሔር ሆይ፤

የበቀል አምላክ ሆይ፤ ደምቀህ ተገለጥ።

2አንተ የምድር ዳኛ ሆይ፤ ተነሥ፤

ለትዕቢተኞች የእጃቸውን ስጣቸው።

3ክፉዎች እስከ መቼ እግዚአብሔር ሆይ፤ ክፉዎች እስከ መቼ ይፈነጫሉ?

4የእብሪት ቃላት ያዥጐደጕዳሉ፤

ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ጕራ ይነዛሉ።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕዝብህን አደቀቁ፤

ርስትህንም አስጨነቁ።

6መበለቲቱንና መጻተኛውን ገደሉ፤

የድኻ ዐደጉንም ነፍስ አጠፉ።

7እነርሱም “እግዚአብሔር አያይም፤

የያዕቆብም አምላክ አያስተውልም” አሉ።

8እናንት በሕዝቡ መካከል ያላችሁ ደነዞች፤ ልብ በሉ፤

እናንት ቂሎች፤ ጥበበኞች የምትሆኑት መቼ ነው?

9ጆሮን የተከለው እርሱ አይሰማምን? ዐይንንስ የሠራ እርሱ አያይምን?

10ሕዝቦችን በተግሣጽ ወደ መንገድ የሚመልስ፣

ዕውቀትንስ ለሰው ልጆች የሚያስተምር አይቀጣምን?

11እግዚአብሔር የሰው ሐሳብ መና፣

ከንቱም እንደ ሆነ ያውቃል።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ የምትገሥጸው፣

ከሕግህም የምታስተምረው ሰው ምስጉን ነው።

13ለኀጢአተኞች ጕድጓድ እስኪማስላቸው ድረስ፣

እርሱን ከመከራ ታሳርፈዋለህ።

14እግዚአብሔር ሕዝቡን አይጥልምና፤

ርስቱንም አይተውም።

15ፍርድ ተመልሶ በጽድቅ አሠራር ላይ ይመሠረታል፤

ልባቸውም ቀና የሆነ ሁሉ ይከተሉታል።

16ክፉዎችን የሚቋቋምልኝ ማን ነው?

ከክፉ አድራጊዎችስ ጋር የሚሟገትልኝ ማን ነው?

17እግዚአብሔር ረዳቴ ባይሆን ኖሮ፣

ነፍሴ ወደ ዝምታው ዓለም ፈጥና በወረደች ነበር።

18እኔ፣ “እግሬ አዳለጠኝ” ባልሁ ጊዜ፣

እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ደግፎ ያዘኝ።

19የውስጤ ጭንቀት በበዛ መጠን፣

ማጽናናትህ ነፍሴን ደስ አሰኛት።

20ዐመፃን ሕጋዊ የሚያደርግ፣

የጥፋት ዙፋን ከአንተ ጋር ሊያብር ይችላልን?

21በጻድቁ ላይ ተሰልፈው ይወጣሉ፤

በንጹሑም ላይ ሞት ይፈርዳሉ።

22ለእኔ ግን እግዚአብሔር ምሽግ፣

አምላኬም መጠጊያ ዐለት ሆኖኛል።

23በደላቸውን ወደ ራሳቸው ይመልሳል፤

በክፋታቸውም ያጠፋቸዋል፤

እግዚአብሔር አምላካችን ይደመስሳቸዋል።

New Serbian Translation

Псалми 94:1-23

Псалам 94

1О, Боже освете!

Севни, Господе, Боже осветниче!

2Устани, судијо земље,

па узврати бахатима истом мером.

3Докле ће зликовци, о, Господе,

докле ће зликовци да ликују?

4Брбљивци су, бахати хвалисавци

сви ти што опако раде.

5Они сатиру твој народ, Господе,

и наследство твоје тлаче.

6Убијају удовицу, дошљака

и сирочад кољу.

7И још кажу: „Господ не види,

не опажа Бог Јаковљев!“

8Размислите, ви свирепи људи! Будале!

Кад ћете се опаметити?

9Не чује ли онај што је творац уха?

Не види ли онај што је творац ока?

10Зар народе он да не кори?

Зар да не покара онај који људе знању учи?

11Господ зна да су мисли човекове безвредне.

12Благо ономе кога ти учиш, Господе,

кога поучаваш о Закону своме;

13да буде спокојан у данима патње,

док се за зликовца јама не ископа.

14Јер Господ не оставља свој народ

и наследства свога он се не одриче.

15Јер праведност се суду враћа

и следе је сва срца честита.

16Ко ће мене да заступа против зликоваца?

Ко ће против злочинаца уз мене да стане?

17Да ми Господ није био помоћ,

убрзо би душа моја у гробу ћутала.

18Када кажем – „Моја нога клеца!“ –

нек ме твоја милост окрепи, Господе!

19Када су у мени самом многобројне бриге,

утехе ми твоје разгаљују душу.

20Зар окрутни владари да ти буду савезници,

и они који крше заповести?

21Уроту праве против душе праведника,

крв невиних осуде ко криву.

22Господ ми је заклон на висини!

Мој је Бог стена уточишта!

23Он ће њима да узврати за злобу њихову,

збрисаће их због зала њихових;

збрисаће их, Господ, Бог наш.