መዝሙር 94 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 94:1-23

መዝሙር 94

የእግዚአብሔር ፍትሕ

1የበቀል አምላክ፣ አንተ እግዚአብሔር ሆይ፤

የበቀል አምላክ ሆይ፤ ደምቀህ ተገለጥ።

2አንተ የምድር ዳኛ ሆይ፤ ተነሥ፤

ለትዕቢተኞች የእጃቸውን ስጣቸው።

3ክፉዎች እስከ መቼ እግዚአብሔር ሆይ፤ ክፉዎች እስከ መቼ ይፈነጫሉ?

4የእብሪት ቃላት ያዥጐደጕዳሉ፤

ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ጕራ ይነዛሉ።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕዝብህን አደቀቁ፤

ርስትህንም አስጨነቁ።

6መበለቲቱንና መጻተኛውን ገደሉ፤

የድኻ ዐደጉንም ነፍስ አጠፉ።

7እነርሱም “እግዚአብሔር አያይም፤

የያዕቆብም አምላክ አያስተውልም” አሉ።

8እናንት በሕዝቡ መካከል ያላችሁ ደነዞች፤ ልብ በሉ፤

እናንት ቂሎች፤ ጥበበኞች የምትሆኑት መቼ ነው?

9ጆሮን የተከለው እርሱ አይሰማምን? ዐይንንስ የሠራ እርሱ አያይምን?

10ሕዝቦችን በተግሣጽ ወደ መንገድ የሚመልስ፣

ዕውቀትንስ ለሰው ልጆች የሚያስተምር አይቀጣምን?

11እግዚአብሔር የሰው ሐሳብ መና፣

ከንቱም እንደ ሆነ ያውቃል።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ የምትገሥጸው፣

ከሕግህም የምታስተምረው ሰው ምስጉን ነው።

13ለኀጢአተኞች ጕድጓድ እስኪማስላቸው ድረስ፣

እርሱን ከመከራ ታሳርፈዋለህ።

14እግዚአብሔር ሕዝቡን አይጥልምና፤

ርስቱንም አይተውም።

15ፍርድ ተመልሶ በጽድቅ አሠራር ላይ ይመሠረታል፤

ልባቸውም ቀና የሆነ ሁሉ ይከተሉታል።

16ክፉዎችን የሚቋቋምልኝ ማን ነው?

ከክፉ አድራጊዎችስ ጋር የሚሟገትልኝ ማን ነው?

17እግዚአብሔር ረዳቴ ባይሆን ኖሮ፣

ነፍሴ ወደ ዝምታው ዓለም ፈጥና በወረደች ነበር።

18እኔ፣ “እግሬ አዳለጠኝ” ባልሁ ጊዜ፣

እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ደግፎ ያዘኝ።

19የውስጤ ጭንቀት በበዛ መጠን፣

ማጽናናትህ ነፍሴን ደስ አሰኛት።

20ዐመፃን ሕጋዊ የሚያደርግ፣

የጥፋት ዙፋን ከአንተ ጋር ሊያብር ይችላልን?

21በጻድቁ ላይ ተሰልፈው ይወጣሉ፤

በንጹሑም ላይ ሞት ይፈርዳሉ።

22ለእኔ ግን እግዚአብሔር ምሽግ፣

አምላኬም መጠጊያ ዐለት ሆኖኛል።

23በደላቸውን ወደ ራሳቸው ይመልሳል፤

በክፋታቸውም ያጠፋቸዋል፤

እግዚአብሔር አምላካችን ይደመስሳቸዋል።

Het Boek

Psalmen 94:1-23

1Jahweh, wrekende God, God der wrake, treed op; 2Verhef U, Rechter der aarde, Vergeld de trotsen wat ze verdienen! 3Hoelang nog zullen de zondaars, o Jahweh, Hoelang nog zullen de boosdoeners juichen? 4Al die booswichten pochen en snoeven, En een hoge toon slaan ze aan! 5Jahweh, ze vertrappen uw volk, En verdrukken uw erfdeel; 6Ze doden weduwen en wezen, Vermoorden die bij ons kwamen wonen. 7En dan zeggen ze nog: Jahweh ziet het niet eens, De God van Jakob merkt het niet! 8Domme kudde, word toch verstandig; Gij dwazen, wanneer wordt gij wijs? 9Zou Hij het niet horen, die het oor heeft geplant, Niet zien, die het oog heeft geschapen; 10Zou Hij, die de volkeren tuchtigt, niet straffen, Onwetend zijn, die den mens onderricht? 11Neen, Jahweh kent de gedachten der mensen, Hij weet, dat het hersenschimmen zijn. 12Jahweh, gelukkig de man, dien Gij onderricht, En dien Gij leert uit uw wet: 13Hoe hij gelaten moet zijn in dagen van rampspoed, Totdat voor den boze het graf is gedolven; 14Hoe Jahweh zijn volk niet verstoot, En nooit zijn erfdeel verlaat; 15Hoe de brave zijn recht weer verkrijgt, Alle oprechten van hart weer geluk! 16Wie anders neemt het voor mij tegen de boosdoeners op, Wie staat mij tegen de booswichten bij? 17Wanneer Jahweh mij niet te hulp was gekomen, Dan lag ik misschien al lang in het graf. 18Maar als ik denk: nú wankelt mijn voet, Dan steunt mij uw goedheid, o Jahweh; 19En wanneer zware zorgen mij innerlijk drukken, Dan verkwikt uw vertroosting mijn ziel. 20Zoudt Gij iets gemeen hebben met de zetel van onrecht, Die onheil sticht op gezag van de wet; 21Met hen, die het leven der braven belagen, En onschuldig bloed durven straffen? 22Neen, voor mij is Jahweh een toevlucht, Mijn God een veilige Rots; 23Maar hùn vergeldt Hij hun onrecht, En vernielt ze om hun boosheid: Jahweh, onze God!