መዝሙር 89
መዝሙርና ለእግዚአብሔር ታማኝነት የቀረበ ጸሎት
የይዝራኤላዊው የኤታን ትምህርት።
1ስለ እግዚአብሔር ምሕረት ለዘለላለም እዘምራለሁ፤
በአፌም ታማኝነትህን ከትውልድ እስከ ትውልድ እገልጻለሁ።
2ምሕረትህን ለዘላለም እንደምትመሠርት፣
ታማኝነትህንም በሰማይ እንደምታጸና እናገራለሁ።
3አንተም እንዲህ ብለሃል፤ “ከመረጥሁት ጋር ኪዳን ገብቻለሁ፤
ለባሪያዬ ለዳዊት ምያለሁ፤
4‘ዘርህን ለዘላለም እተክላለሁ፤
ዙፋንህንም ከትውልድ እስከ ትውልድ አጸናለሁ።’ ” ሴላ
5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሰማያት ድንቅ ሥራህን፣
ታማኝነትህንም በቅዱሳን ጉባኤ መካከል ያወድሳሉ፤
6በላይ በሰማያት ከእግዚአብሔር ጋር ማን ሊስተካከል ይችላል?
ከሰማያውያን ፍጥረታትስ መካከል ማን እግዚአብሔርን ይመስለዋል?
7እግዚአብሔር በቅዱሳን ጉባኤ መካከል በጣም የሚፈራ፣
በዙሪያውም ካሉት ሁሉ በላይ እጅግ የሚከበር ነው።
8የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ አንተ ያለ ማን ነው?
እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ኀያል ነህ፤ ታማኝነትህም ከብቦሃል።
9የባሕርን ቍጣ ትቈጣጠራለህ፤
ሞገዱም ሲነሣ ጸጥ ታደርገዋለህ።
10አንተ ረዓብን የተሰየፈ ያህል አደቀቅኸው፤
በብርቱ ክንድህም ጠላቶችህን በተንሃቸው።
11ሰማያት የአንተ ናቸው፤ ምድርም የአንተ ናት፤
ዓለምንና በውስጧ ያለውን ሁሉ አንተ መሠረትህ።
12ሰሜንንና ደቡብን የፈጠርህ አንተ ነህ፤
ታቦርና አርሞንዔም በስምህ ሐሤት ያደርጋሉ።
13አንተ ክንደ ብርቱ ነህ፤
እጅህ ኀያል ናት፤ ቀኝ እጅህም ከፍ ከፍ ያለች ናት።
14ጽድቅና ፍትሕ የዙፋንህ መሠረቶች ናቸው፤
ምሕረትና ታማኝነት በፊትህ ይሄዳሉ።
15እግዚአብሔር ሆይ፤ እልልታን የሚያውቅ፣
በፊትህም ብርሃን የሚሄድ ሕዝብ ምስጉን ነው።
16ቀኑን ሙሉ በስምህ ደስ ይላቸዋል፤
በጽድቅህም ሐሤት ያደርጋሉ፤
17አንተ የብርታታቸው ክብር ነህና፤
በሞገስህም ቀንዳችንን89፥17 የጥንካሬ ምልክት ነው። ከፍ ከፍ አደረግህ።
18ጋሻችን89፥18 ወይም ልዑል ማለት ነው። የእግዚአብሔር ነውና፤
ንጉሣችንም የራሱ የእስራኤል ቅዱስ ነው።
19በዚያን ጊዜ በራእይ ተናገርህ፤
ታማኝ ሕዝብህንም እንዲህ አልህ፤
“ኀያሉን ሰው ሥልጣን አጐናጸፍሁት፤
ከሕዝብ መካከል የተመረጠውንም ከፍ ከፍ አደረግሁት።
20ባሪያዬን ዳዊትን አገኘሁት፤
በተቀደሰው ዘይቴም ቀባሁት።
21እጄ ይደግፈዋል፤
ክንዴም ያበረታዋል።
22በጠላት አይበለጥም፤
ክፉ ሰውም አይበግረውም።
23ባላንጣዎቹን በፊቱ አደቅቃቸዋለሁ፤
ጠላቶቹንም እቀጠቅጣለሁ።
24ታማኝነቴና ምሕረቴ ከእርሱ ጋር ይሆናል፤
በስሜም ቀንዱ ከፍ ከፍ ይላል።
25እጁን በባሕር ላይ፣
ቀኝ እጁንም በወንዞች ላይ አኖራለሁ።
26እርሱም፣ ‘አንተ አባቴ ነህ፤
አምላኬና መዳኛ ዐለቴም ነህ’ ብሎ ይጠራኛል።
27እኔም ደግሞ በኵሬ አደርገዋለሁ፤
ከምድር ነገሥታትም በላይ ከፍ ይላል።
28ምሕረቴንም ለዘላለም ለእርሱ እጠብቃለሁ፤
ከእርሱ ጋር የገባሁት ኪዳንም ጸንቶ ይኖራል።
29የዘር ሐረጉን ለዘላለም፣
ዙፋኑንም በሰማያት ዕድሜ ልክ አጸናለሁ።
30“ልጆቹ ሕጌን ቢተዉ፣
ደንቤን ባይጠብቁ፣
31ሥርዐቴን ቢጥሱ፣
ትእዛዜንም ባያከብሩ፣
32ኀጢአታቸውን በበትር፣
በደላቸውን በጅራፍ እቀጣለሁ።
33ምሕረቴን ግን ከእርሱ አላርቅም፤
ታማኝነቴንም አላጓድልበትም።
34ኪዳኔን አላፈርስም፤
ከአፌ የወጣውንም አላጥፍም።
35አንድ ጊዜ በቅድስናዬ ምያለሁና፣
ዳዊትን አልዋሸውም።
36የዘር ሐረጉ ለዘላለም፣
ዙፋኑም በፊቴ እንደ ፀሓይ ጸንቶ ይኖራል፤
37በሰማይ ታማኝ ምስክር ሆና እንደምትኖረው፣
እንደ ጨረቃ እርሱ ለዘላለም ይመሠረታል።” ሴላ
38አሁን ግን ናቅኸው፤ ጣልኸውም፤
የቀባኸውንም እጅግ ተቈጣኸው።
39ከባሪያህ ጋር የገባኸውን ኪዳን አፈረስህ፤
የክብር ዘውዱን ትቢያ ላይ ጥለህ አቃለልኸው።
40ቅጥሩን ሁሉ አፈራረስህ፤
ምሽጉንም ደመሰስህ።
41ዐላፊ አግዳሚው ሁሉ ዘረፈው፤
ለጎረቤቶቹ መዘባበቻ ሆነ።
42የጠላቶቹን ቀኝ እጅ ከፍ ከፍ አደረግህ፤
ባላንጣዎቹም ሁሉ ደስ አላቸው።
43የሰይፉን ስለት አጠፍህ፤
በጦርነትም ጊዜ አልረዳኸውም።
44ግርማዊነቱን አጠፋህበት፤
ዙፋኑንም ከዐፈር ደባለቅኸው።
45የወጣትነት ዘመኑን አሳጠርኸው፤
ዕፍረትንም አከናነብኸው። ሴላ
46እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህ እስከ መቼ ይሆናል? ራስህንስ ለዘላለም ትሰውራለህን?
ቍጣህስ እንደ እሳት የሚነድደው እስከ መቼ ነው?
47ዘመኔ ምን ያህል ዐጭር እንደ ሆነች ዐስብ፤
የሰውን ልጆች እንዲያው ለከንቱ ፈጠርሃቸው!
48ሞትን ሳያይ ሕያው ሆኖ የሚቀር
ሰው አለን?
ራሱን ከሲኦል እጅ ማዳን የሚችል ማን ነው? ሴላ
49ጌታ ሆይ፤ ለዳዊት በታማኝነትህ የማልህለት፣
የቀድሞው ምሕረትህ የት አለ?
50ጌታ ሆይ፤ ባሪያህ89፥50 ባሮችህ የሚሉ አሉ። እንዴት እንደ ተፌዘበት፣
የብዙ ሰዎችንም ነቀፋ እንደ ታቀፍሁ ዐስብ።
51እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶችህ የተሣለቁበትን፣
የቀባኸውን ሰው ርምጃ የነቀፉበትን ሁኔታ ዐስብ።
52እግዚአብሔር ለዘላለም ይባረክ፤
አሜን፤ አሜን።
Четвёртая книга
Песнь 89
1Молитва пророка Мусы.
2Владыка, Ты был для нас прибежищем
из поколения в поколение.
3Прежде чем родились горы
и Ты образовал землю и весь мир,
от века и до века Ты – Бог.
4Ты возвращаешь человека в тление
и говоришь: «Вернитесь, смертные».
5Тысяча лет в глазах Твоих, как день вчерашний, что минул,
как несколько часов в ночи.
6Как наводнением уносишь людей;
они проходят, как сон.
Они – как трава, что утром взошла:
утром она цветёт и зеленеет,
а вечером вянет и засыхает.
7Мы исчезаем от Твоего гнева,
мы в смятении от Твоей ярости.
8Ты поставил наши беззакония перед Собою
и наши тайные грехи – перед лицом Своим.
9Наши дни проходят в Твоём гневе;
мы завершаем свои годы со стоном.
10Дней нашей жизни – лет семьдесят,
а для тех, кто покрепче, – лет восемьдесят,
и большая часть их – труд и скорбь;
быстро они проходят, и мы исчезаем.
11Кто познал силу Твоего гнева?
Ярость Твоя столь же велика,
сколь велик страх перед Тобой.
12Научи нас вести счёт нашим дням,
чтобы мы обрели сердце мудрое.
13Возвратись, Вечный! Как долго ещё будешь гневаться?
Сжалься над Своими рабами!
14Насыщай нас по утрам милостью Своей,
чтобы мы радовались и веселились все наши дни.
15Возвесели нас за дни, когда Ты наказывал нас,
и за годы, в которые мы испытывали бедствие.
16Да откроется взору рабов Твоих дело Твоё,
и слава Твоя – их детям.
17И да пребудет на нас милость Владыки, нашего Бога.
Укрепи наше дело,
укрепи для нас дело наших рук.