መዝሙር 80 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 80:1-19

መዝሙር 80

ለእስራኤል ተሐድሶ የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ “የኪዳን ጽጌረዳ” በሚለው ቅኝት የሚዜም፤ የአሳፍ መዝሙር።

1ዮሴፍን እንደ በግ መንጋ የምትመራ፣

የእስራኤል እረኛ ሆይ፤ ስማን፤

በኪሩቤል ላይ በዙፋን የምትቀመጥ ሆይ፤

በብርሃንህ ተገለጥ።

2በኤፍሬም፣ በብንያምና በምናሴ ፊት ደምቀህ ታይ።

ኀይልህን አንቀሳቅስ፤

መጥተህም አድነን።

3አምላክ ሆይ፤ መልሰን፤

እንድንም ዘንድ፣

ፊትህን አብራልን።

4የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤

በሕዝብህ ጸሎት ላይ ቍጣህ የሚነድደው፣

እስከ መቼ ድረስ ነው?

5የእንባ እንጀራ አበላሃቸው፤

ስፍር የሞላ እንባም አጠጣሃቸው።

6ለጎረቤቶቻችን የጠብ ምክንያት አደረግኸን፤

ጠላቶቻችንም ተሣሣቁብን።

7የሰራዊት አምላክ ሆይ፤ መልሰን፤

እንድንም ዘንድ፣

ፊትህን አብራልን።

8ከግብፅ የወይን ግንድ አመጣህ፤

አሕዛብን አባርረህ እርሷን ተከልሃት።

9መሬቱን መነጠርህላት፤

እርሷም ሥር ሰድዳ አገሩን ሞላች።

10ተራሮች በጥላዋ ተሸፈኑ፤

ግዙፍ ዝግቦችም በቅርንጫፎቿ ተጠለሉ።

11ቅርንጫፎቿን እስከ ባሕሩ፣80፥11 ሜድትራኒያን ሳይሆን አይቀርም።

ቍጥቋጦዋንም እስከ ወንዙ80፥11 የኤፍራጥስ ወንዝ ለማለት ነው። ዘረጋች።

12ታዲያ ዐላፊ አግዳሚው ፍሬዋን እንዲለቅም፣

ለምን ቅጥሯን አፈረስህ?

13ዕርያ ከዱር ወጥቶ ያበለሻሻታል፤

በሜዳ የሚንጋጋ እንስሳ ሁሉ ይበላታል።

14የሰራዊት አምላክ ሆይ፤ እንግዲህ ወደ እኛ ተመለስ፤

ከሰማይ ተመልከት፤ እይም፤

ይህችን የወይን ተክል ተንከባከባት፤

15ይህች ቀኝ እጅህ የተከላት ቡቃያ፣

ለራስህ ያጸደቅሃት ተክል80፥15 ወንድ ልጅ የሚሉ ትርጕሞች አሉ። ናት።

16እርሷም በእሳት ተቃጥላለች፤

የግንባርህ ተግሣጽ ያጠፋቸዋል።

17ለራስህ ባበረታኸው የሰው ልጅ ላይ፣

በቀኝ እጅህ ሰው ላይ እጅህ ትሁን።

18ከእንግዲህ አንተን ትተን ወደ ኋላ አንመለስም፤

ሕያዋን አድርገን፤ እኛም ስምህን እንጠራለን።

19የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ መልሰን፤

እንድንም ዘንድ፣

ፊትህን አብራልን።

New International Version

Psalms 80:1-19

Psalm 80In Hebrew texts 80:1-19 is numbered 80:2-20.

For the director of music. To the tune of “The Lilies of the Covenant.” Of Asaph. A psalm.

1Hear us, Shepherd of Israel,

you who lead Joseph like a flock.

You who sit enthroned between the cherubim,

shine forth 2before Ephraim, Benjamin and Manasseh.

Awaken your might;

come and save us.

3Restore us, O God;

make your face shine on us,

that we may be saved.

4How long, Lord God Almighty,

will your anger smolder

against the prayers of your people?

5You have fed them with the bread of tears;

you have made them drink tears by the bowlful.

6You have made us an object of derision80:6 Probable reading of the original Hebrew text; Masoretic Text contention to our neighbors,

and our enemies mock us.

7Restore us, God Almighty;

make your face shine on us,

that we may be saved.

8You transplanted a vine from Egypt;

you drove out the nations and planted it.

9You cleared the ground for it,

and it took root and filled the land.

10The mountains were covered with its shade,

the mighty cedars with its branches.

11Its branches reached as far as the Sea,80:11 Probably the Mediterranean

its shoots as far as the River.80:11 That is, the Euphrates

12Why have you broken down its walls

so that all who pass by pick its grapes?

13Boars from the forest ravage it,

and insects from the fields feed on it.

14Return to us, God Almighty!

Look down from heaven and see!

Watch over this vine,

15the root your right hand has planted,

the son80:15 Or branch you have raised up for yourself.

16Your vine is cut down, it is burned with fire;

at your rebuke your people perish.

17Let your hand rest on the man at your right hand,

the son of man you have raised up for yourself.

18Then we will not turn away from you;

revive us, and we will call on your name.

19Restore us, Lord God Almighty;

make your face shine on us,

that we may be saved.