መዝሙር 63 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 63:1-11

መዝሙር 63

እግዚአብሔርን መፈለግ

በይሁዳ ምድረ በዳ በነበረ ጊዜ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ አምላኬ ነህ፤

አንተን ከልብ እሻለሁ፤ ውሃ በሌለበት፣

በደረቅና በተራቈተ ምድር፣

ነፍሴ አንተን ተጠማች፤

ሥጋዬም አንተን ናፈቀች።

2ስለዚህ በመቅደስ ውስጥ አየሁህ፤

ኀይልህንና ክብርህንም ተመለከትሁ።

3ምሕረትህ ከሕይወት ይበልጣልና፤

ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል።

4እንግዲህ፣ በሕይወቴ ዘመን አመሰግንሃለሁ፤

በአንተም ስም እጆቼን አነሣለሁ።

5ነፍሴ በቅቤና በሥብ እንደሚረካ ሰው ትረካለች፤

አፌም በሚያዜሙ ከንፈሮች በደስታ ያወድስሃል።

6በመኝታዬ ዐስብሃለሁ፤

ሌሊቱንም ሁሉ ስለ አንተ አሰላስላለሁ።

7አንተ ረዳቴ ነህና፣

በክንፎችህ ሥር ተጠልዬ በደስታ እዘምራለሁ።

8ነፍሴ አንተን የሙጥኝ ብላለች፤

ቀኝ እጅህም ደግፋ ይዛኛለች።

9ነፍሴን ለማጥፋት የሚሹ ግን፣

ወደ ምድር ጥልቅ ይወርዳሉ፤

10ለሰይፍ ዐልፈው ይሰጣሉ፤

የቀበሮዎችም ምግብ ይሆናሉ።

11ንጉሥ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል፤

በእግዚአብሔርም ስም ቃል የሚገቡ ሁሉ ይከብራሉ፤

የሐሰተኞች አንደበትም ትዘጋለች።

New International Version – UK

Psalms 63:1-11

Psalm 63In Hebrew texts 63:1-11 is numbered 63:2-12.

A psalm of David. When he was in the Desert of Judah.

1You, God, are my God,

earnestly I seek you;

I thirst for you,

my whole being longs for you,

in a dry and parched land

where there is no water.

2I have seen you in the sanctuary

and beheld your power and your glory.

3Because your love is better than life,

my lips will glorify you.

4I will praise you as long as I live,

and in your name I will lift up my hands.

5I will be satisfied as with the richest of foods;

with singing lips my mouth will praise you.

6On my bed I remember you;

I think of you through the watches of the night.

7Because you are my help,

I sing in the shadow of your wings.

8I cling to you;

your right hand upholds me.

9Those who want to kill me will be destroyed;

they will go down to the depths of the earth.

10They will be given over to the sword

and become food for jackals.

11But the king will rejoice in God;

all who swear by God will glory in him,

while the mouths of liars will be silenced.