መዝሙር 53 – NASV & CARS

New Amharic Standard Version

መዝሙር 53:1-6

መዝሙር 53

አምላክ የለሾች

53፥1-6 ተጓ ምብ – መዝ 14፥1-7

ለመዘምራን አለቃ፤ በማኸላት፤ የዳዊት ትምህርት53 ርእሱ ምናልባት የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1ቂል በልቡ፣

“እግዚአብሔር የለም” ይላል።

ብልሹዎች ናቸው፤ ተግባራቸውም ጸያፍ ነው፤

በጎ ነገርን የሚያደርግ አንድ እንኳ የለም።

2በማስተዋል የሚመላለስ፣

እግዚአብሔርን የሚፈልግ እንዳለ ለማየት፣

እግዚአብሔር ከሰማይ

ወደ ሰው ልጆች ተመለከተ።

3ሁሉም ወደ ሌላ ዘወር አሉ፤

በአንድነትም ተበላሹ፤

አንድ እንኳ

በጎ የሚያደርግ የለም።

4ሰው እንጀራ እንደሚበላ ሕዝቤን የሚበሉት፣

እግዚአብሔርንም ጠርተው የማያውቁት፣

እነዚያ ክፉ አድራጊዎች ከቶ አይማሩምን?

5የሚያስፈራ ነገር በሌለበት፣

በዚያ፣ በፍርሀት ተዋጡ፤

እግዚአብሔር የዘመቱብህን ሰዎች ዐጥንት በተነ፤

እርሱ እግዚአብሔር ስለ ናቃቸው፣ አንተ አሳፈርሃቸው።

6ምነው ለእስራኤል የሚሆን መዳን ከጽዮን በወጣ!

እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣

ያዕቆብ ሐሤት ያድርግ፤ እስራኤል ደስ ይበለው።

Священное Писание

Забур 53:1-9

Песнь 53

1Дирижёру хора. На струнных инструментах. Наставление Давуда, 2когда зифиты пришли и сказали Шаулу: «У нас скрывается Давуд»53:2 См. 1 Цар. 23:19-28; 26:1-2..

3Всевышний, спаси меня Своим именем;

оправдай меня Своей силой!

4Всевышний, услышь молитву мою;

внемли моим словам!

5Чужие восстали против меня,

беспощадные желают моей смерти –

те, кто не думает о Всевышнем. Пауза

6Но Всевышний – помощник мне;

Владыка меня укрепляет.

7Он воздаст врагам моим за зло,

погубит их ради Своей верности.

8Я добровольно принесу Тебе жертву.

Вечный, я буду славить имя Твоё,

потому что оно прекрасно.

9Ведь Ты уберёг меня от всех бед,

и я видел поражение моих врагов.