መዝሙር 5 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 5:1-12

መዝሙር 5

የጧት ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በዋሽንት የሚዘመር፣ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ቃሌን አድምጥ፤

መቃተቴንም ቸል አትበል።

2ንጉሤና አምላኬ ሆይ፤

ወደ አንተ እጸልያለሁና፣

ድረስልኝ ብዬ ስጮኽ ስማኝ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ በማለዳ ድምፄን ትሰማለህ፤

በማለዳ ልመናዬን በፊትህ አቀርባለሁ፤

ፈቃድህንም በጥሞና እጠባበቃለሁ፤

4አንተ በክፋት ደስ የምትሰኝ አምላክ አይደለህም፤

ክፉም ከአንተ ጋር አያድርም።

5እብሪተኞች በፊትህ መቆም አይችሉም፤

ክፉ አድራጊዎችንም ሁሉ ጠላህ።

6ሐሰት የሚናገሩትን ታጠፋቸዋለህ፤

ደም የተጠሙትንና አታላዮችን፣

እግዚአብሔር ይጸየፋቸዋል።

7እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት

ወደ ቤትህ እገባለሁ፤

አንተንም በመፍራት፣

ወደ ተቀደሰው መቅደስህ እሰግዳለሁ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ ከጠላቶቼ የተነሣ፣

በጽድቅህ ምራኝ፤

መንገድህንም በፊቴ አቅናልኝ።

9በንግግራቸው ውስጥ እውነት የለም፤

ልባቸው የጥፋት ጐሬ ነው፤

ጕረሯቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤

በምላሳቸውም ይሸነግላሉ።

10አምላክ ሆይ፤ የእጃቸውን ስጣቸው!

ተንኰላቸው መውደቂያቸው ይሁን፤

ከኀጢአታቸው ብዛት የተነሣ አስወግዳቸው፣

በአንተ ላይ ዐምፀዋልና።

11አንተን መጠጊያ የሚያደርጉ ሁሉ ግን ደስ ይበላቸው፤

ዘላለም በደስታ ይዘምሩ፤

ስምህን የሚወድዱ በአንተ ደስ እንዲላቸው፣

ተከላካይ ሁንላቸው።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቃንን ትባርካቸዋለህ፤

በሞገስህም እንደ ጋሻ ትከልላቸዋለህ።

Het Boek

Psalmen 5:1-12

1Voor muziekbegeleiding: met fluiten. Een psalm van David. Jahweh, hoor naar mijn roepen, Let op mijn zuchten; 2Luister naar mijn schreien, Mijn Koning en God. 3Want tot U richt ik mijn bede, o Jahweh, Reeds in de vroegte hoort Gij mijn smeken; ‘s Morgens leg ik het voor U neer, En zie vertrouwend naar U op. 4Gij zijt geen God, wien de boosheid behaagt, Nooit is de zondaar U welkom; 5Geen goddeloze mag Voor uw ogen verschijnen! Gij haat al wie ongerechtigheid pleegt, 6En leugenaars richt Gij te gronde; De man van bloed en bedrog Is een afschuw voor Jahweh. 7Maar door uw grote genade Mag ìk uw huis binnengaan, En naar uw heilige tempel gericht, U vol eerbied aanbidden. 8Geleid mij, o Jahweh, Naar uw gerechtigheid; En om wille van die mij belagen, Baan mij de weg voor uw aanschijn. 9Neen, in hun mond is geen waarheid, En hun hart is bedorven; Een open graf is hun keel, Ze huichelen met hun tong. 10Laat ze boeten, o God, Aan eigen sluwheid te gronde gaan; Stoot ze weg om hun talrijke zonden, Want ze zijn weerbarstig tegen U. 11Dan verheugen zich allen, Die tot U vluchten; Jubelen eeuwig, Daar Gij ze beschermt; En juichen in U, Die uw Naam beminnen. 12Want Gij zegent den rechtvaardige, Jahweh; Als een schild dekt hem uw liefde.