መዝሙር 46 – NASV & CARSA

New Amharic Standard Version

መዝሙር 46:1-11

መዝሙር 4646 ርእስ ምናልባት የሙዚቃውን ሁኔታ ሊያሳይ ይችላል።

እግዚአብሔር ከእኛ ጋር

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር፤ በደናግል የዜማ ስልት የሚዘመር መዝሙር።

1አምላካችን መጠጊያችንና ኀይላችን፣

በሚደርስብን መከራ ሁሉ የቅርብ ረዳታችን ነው።

2ስለዚህ ምድር ብትነዋወጥ እንኳ፣

ተራሮችም ወደ ባሕር ጥልቅ ቢሰምጡ አንፈራም።

3ውሆች ቢያስገመግሙ፣ ዐረፋ ቢደፍቁም፣ ተራሮችም ከውሆቹ ሙላት የተነሣ

ቢንቀጠቀጡም አንደናገጥም። ሴላ

4የእግዚአብሔርን ከተማ፣

የልዑልን የተቀደሰ ማደሪያ ደስ የሚያሰኙ የወንዝ ፈሳሾች አሉ።

5እግዚአብሔር በመካከሏ ነው፤ አትናወጥም፤

አምላክ በማለዳ ይረዳታል።

6ሕዝቦች በዐመፅ ተነሡ፤ መንግሥታትም ወደቁ፤

ድምፁን ከፍ አድርጎ አሰማ፤ ምድርም ቀለጠች።

7የሰራዊት አምላክ ከእኛ ጋር ነው፤

የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ

8ኑና የእግዚአብሔርን ሥራ፣

ምድርንም እንዴት ባድማ እንዳደረጋት እዩ።

9ከዳር እስከ ዳር ጦርነትን ከምድር ያስወግዳል፤

ቀስትን ይሰብራል፤ ጦርን ያነክታል፤

ጋሻንም46፥9 ወይም ሠረገላንም በእሳት ያቃጥላል።

10“ዕረፉ፤ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ ዕወቁ፤

በሕዝቦች ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፤

በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።”

11የሰራዊት አምላክ ከእኛ ጋር ነው፤

የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ

Священное Писание (Восточный перевод), версия с «Аллахом»

Забур 46:1-10

Песнь 46

1Дирижёру хора. Песнь потомков Кораха.

2Рукоплещите, все народы,

вознесите Аллаху крик радости.

3Как грозен Вечный, Высочайший,

великий Царь над всей землёй!

4Он покорил нам народы,

ногами мы попираем племена.

5Он избрал нам наследие –

гордость Якуба, которого Он возлюбил. Пауза

6Аллах вознёсся под крики радости;

Вечный вознёсся под звуки рогов.

7Пойте Аллаху хвалу, пойте!

Пойте хвалу нашему Царю, пойте!

8Аллах – Царь над всей землёй;

пойте Ему искусную песнь.

9Аллах царит над народами;

Аллах восседает на святом престоле Своём.

10Собираются вожди народов

вместе с народом Бога Ибрахима,

ведь земные правители46:10 Букв.: «щиты». принадлежат Аллаху;

Он высоко превознесён над ними.