መዝሙር 45 – NASV & CARS

New Amharic Standard Version

መዝሙር 45:1-17

መዝሙር 45

የንጉሣዊ ሰርግ መዝሙር

ለመዘምራን አለቃ፤ “በጽጌረዳ” ዜማ፤ የቆሬ ልጆች ትምህርት፤ የፍቅር መዝሙር45 የሥነ ጽሑፉን ቅርጽ ወይም የመዝሙሩን ሁኔታ የሚያሳይ ሊሆን ይችላል።

1ልቤ መልካም ሐሳብ አፈለቀ፤

የተቀኘሁትን ቅኔ ለንጉሥ አሰማለሁ፤

አንደበቴም እንደ ባለሙያ ጸሓፊ ብርዕ ነው።

2አንተ ከሰዎች ሁሉ ይልቅ ውብ ነህ፤

ከንፈሮችህም የጸጋ ቃል ያፈልቃሉ፤

ስለዚህ እግዚአብሔር ለዘላለም ባርኮሃል።

3ኀያል ሆይ፤ ሰይፍህን በወገብህ ታጠቅ፤

ግርማ ሞገስንም ተላበስ።

4ስለ እውነት፣ ስለ ትሕትና፣ ስለ ጽድቅ

ሞገስን ተጐናጽፈህ በድል አድራጊነት ገሥግሥ፤

ቀኝ እጅህም ድንቅ ተግባር ታሳይ።

5የሾሉ ፍላጻዎችህ በንጉሥ ጠላቶች ልብ ይሰካሉ፤

ሕዝቦችም ከእግርህ በታች ይወድቃሉ።

6አምላክ ሆይ፤ ዙፋንህ ከዘላለም እስከ ዘላለም ይኖራል፤

የመንግሥትህ በትር የቅንነት በትር ናት።

7ጽድቅን ወደድህ፤ ዐመፃን ጠላህ፤

ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክህ፣

ከጓደኞችህ ይልቅ አንተን የደስታ ዘይት ቀባህ።

8ልብስህ ሁሉ በከርቤ፣ በአደስና በጥንጁት መዐዛ ያውዳል፤

በዝኆን ጥርስ ከተዋቡ ቤተ መንግሥቶችም፣

የበገናና የመሰንቆ ድምፅ ደስ ያሰኙሃል።

9ከተከበሩት ሴቶችህ መካከል የነገሥታት ሴቶች ልጆች ይገኛሉ፤

ንግሥቲቱም በኦፊር ወርቅ አጊጣ በቀኝህ ቆማለች።

10ልጄ ሆይ፤ አድምጪ፤ አስተውዪ፤ ጆሮሽንም አዘንብዪ፤

ሕዝብሽንና የአባትሽን ቤት እርሺ።

11ንጉሥ በውበትሽ ተማርኳል፤

ጌታሽ ነውና አክብሪው።

12የጢሮስ ሴት ልጅ እጅ መንሻ ይዛ ትመጣለች፤45፥12 ወይም፣ የጢሮሳውያን ልብሰ ተክህኖ ከስጦታዎቹ መካከል አለ

ሀብታሞችም ደጅ ይጠኑሻል።

13የንጉሥ ልጅ ከላይ እስከ ታች ተሸልማ እልፍኟ ውስጥ አለች፤

ልብሷም ወርቀ ዘቦ ነው።

14በጥልፍ ሥራ ባጌጠ ልብስ ወደ ንጉሥ ትወሰዳለች፤

ደናግል ጓደኞቿም ተከትለዋት፣

ወደ አንተ ይመጣሉ።

15በደስታና በሐሤት ወደ ውስጥ ይመሯቸዋል፤

ወደ ንጉሡም ቤተ መንግሥት ይገባሉ።

16ወንዶች ልጆችህ በአባቶችህ እግር ይተካሉ፤

ገዦችም አድርገሽ በምድር ሁሉ ትሾሚያቸዋለሽ።

17ስምሽን በትውልድ ሁሉ ዘንድ መታሰቢያ አደርጋለሁ፤

ስለዚህ ሕዝቦች ከዘላለም እስከ ዘላለም ያወድሱሃል።

Священное Писание

Забур 45:1-12

Песнь 45

1Дирижёру хора. Под аламот45:1 Аламот – неизвестный музыкальный термин, обозначающий, вероятнее всего, определённый стиль или верхний звуковой регистр.. Песнь потомков Кораха.

2Всевышний – прибежище нам и сила,

верный помощник в бедах.

3Потому и не устрашимся мы,

пусть даже дрогнет сама земля,

и горы обрушатся в бездну моря,

4пусть воды морские ревут и пенятся,

и горы дрожат от их волнения. Пауза

5Речные потоки радуют город Всевышнего45:5 То есть Иерусалим.,

святое жилище Высочайшего.

6Всевышний в этом городе, и он не падёт;

Всевышний поддерживает его с раннего утра.

7Народы мятутся, и царства рушатся;

подаёт Он Свой голос – и тает земля.

8С нами Вечный, Повелитель Сил;

Бог Якуба – наша крепость. Пауза

9Придите, посмотрите на дела Вечного,

какие опустошения Он произвёл на земле.

10До краёв земли прекращает Он войны,

ломает луки и копья

и сжигает дотла щиты45:10 Или: «колесницы»..

11Он говорит: «Остановитесь, познайте, что Я – Бог;

Я прославлюсь в народах,

прославлюсь на земле».

12С нами Вечный, Повелитель Сил;

Бог Якуба – наша крепость. Пауза