መዝሙር 42 – NASV & CARS

New Amharic Standard Version

መዝሙር 42:1-11

ሁለተኛ መጽሐፍ

ከመዝሙር 42–72

መዝሙር 4242 በብዙ የዕብራይስጥ ቅጆች መዝሙር 42 እና 43 አንድ መዝሙር ነው።

ለመዘምራን አለቃ።

በስደት ላይ ያለ ሌዋዊ ልቅሶ

1ዋላ የምንጭ ውሃ እንደምትናፍቅ፣

አምላክ ሆይ፤ ነፍሴም እንዲሁ አንተን ትናፍቃለች።

2ነፍሴ አምላክን፣ ሕያው አምላክን ተጠማች፤

መቼ ደርሼ ነው የአምላክን ፊት የማየው?

3ሰዎች ቀኑን ሙሉ፣

“አምላክህ የት አለ?” ባሉኝ ቍጥር፣

እንባዬ ቀንና ሌሊት፣

ምግብ ሆነኝ።

4ነፍሴ በውስጤ እየፈሰሰች፣

እነዚህን ነገሮች አስታወስሁኝ፤

ታላቅ ሕዝብ ወደ እግዚአብሔር ቤት እየመራሁ፣

በእልልታና በምስጋና መዝሙር፣

በአእላፍ ሕዝብ መካከል፣

እንዴት ከሕዝቡ ጋር እሄድ እንደ ነበር ትዝ አለኝ።

5ነፍሴ ሆይ፤ ለምን ትተክዢያለሽ?

ለምንስ በውስጤ ትታወኪያለሽ?

ተስፋሽን በአምላክ ላይ አድርጊ፤

6አዳኜና አምላኬን፣ ገና አመሰግነዋለሁና።

ነፍሴ በውስጤ ተክዛለች፤

ስለዚህ በዮርዳኖስ ምድር፣

በአርሞንኤም ከፍታ፣ በሚዛር ተራራ ዐስብሃለሁ።

7በፏፏቴህ ማስገምገም፣

አንዱ ጥልቅ ሌላውን ጥልቅ ይጣራል፤

ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ፣

ሙሉ በሙሉ አጥለቀለቀኝ።

8እግዚአብሔር ምሕረቱን በቀን ያዝዛል፤

ዝማሬውም በሌሊት በእኔ ዘንድ አለ፤

ይህም ለሕይወቴ አምላክ የማቀርበው ጸሎት ነው።

9እግዚአብሔር ዐለቴን፣

“ለምን ረሳኸኝ?

ጠላትስ እያስጨነቀኝ፣

ለምን በሐዘን እመላለሳለሁ?” እለዋለሁ።

10ጠላቶቼ ቀኑን ሙሉ፣

“አምላክህ የት አለ?” እያሉ፣

በነገር ጠዘጠዙኝ፣

ዐጥንቴም ደቀቀ።

11ነፍሴ ሆይ፤ ለምን ትተክዢያለሽ?

ለምንስ በውስጤ ትታወኪያለሽ?

ተስፋሽን በአምላክ ላይ አድርጊ፣

አዳኜና አምላኬን

ገና አመሰግነዋለሁና።

Священное Писание

Забур 42:1-5

Песнь 42

1Оправдай меня, Всевышний;

вступись в мою тяжбу с народом безбожным;

от лживых и несправедливых спаси меня.

2Ты – Всевышний, крепость моя.

Почему Ты отверг меня?

Почему я скитаюсь, плача,

оскорблённый моим врагом?

3Пошли Свой свет и истину –

пусть они меня направляют;

пусть приведут на святую гору Твою,

к месту, где Ты обитаешь.

4Тогда приду я к жертвеннику Всевышнего,

к Богу радости и веселья моего.

Буду славить Тебя на арфе,

Всевышний, мой Бог.

5Что унываешь, моя душа?

Зачем тревожишься?

Возложи надежду на Всевышнего,

ведь я ещё буду славить Его –

моего Спасителя и моего Бога.