መዝሙር 4 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 4:1-8

መዝሙር 4

የሠርክ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዜም የዳዊት መዝሙር።

1የጽድቄ አምላክ ሆይ፤

በጠራሁህ ጊዜ መልስልኝ፤

ከጭንቀቴ አሳርፈኝ፤

ማረኝ፤ ጸሎቴንም ስማ።

2ሰዎች ሆይ፤ እስከ መቼ ድረስ ክብሬን ዝቅ4፥2 ወይም ወደ ራሳችሁ ታደርጋላችሁ?

እስከ መቼስ ድረስ ከንቱ ነገርን ትወድዳላችሁ? ሐሰትንስ4፥2 ወይም የሐሰት አማልክት ትሻላችሁ? ሴላ

3እግዚአብሔር ጻድቁን ለራሱ እንደ ለየ ዕወቁ፤

እግዚአብሔር ወደ እርሱ በተጣራሁ ጊዜ ይሰማኛል።

4ስትቈጡ ኀጢአት አትሥሩ፤

በዐልጋችሁም ላይ ሳላችሁ፣

ልባችሁን መርምሩ፤ ጸጥም በሉ። ሴላ

5የጽድቅን መሥዋዕት አቅርቡ፤

በእግዚአብሔርም ታመኑ።

6ብዙዎች፣ “አንዳች በጎ ነገር ማን ያሳየናል?” ይላሉ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ የፊትህ ብርሃን በላያችን ይብራ።

7ስንዴና አዲስ የወይን ጠጅ በብዛት ባመረቱ ጊዜ ከሚያገኙት ደስታ ይልቅ፣

አንተ ልቤን በታላቅ ሐሤት ሞልተኸዋል።

8በሰላም እተኛለሁ፤ አንቀላፋለሁም፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ያለ ሥጋት የምታሳድረኝ አንተ ብቻ ነህና።

New International Reader’s Version

Psalm 4:1-8

Psalm 4

For the director of music. A psalm of David to be played on stringed instruments.

1My faithful God,

answer me when I call out to you.

Give me rest from my trouble.

Have mercy on me. Hear my prayer.

2How long will you people turn my glory into shame?

How long will you love what will certainly fail you?

How long will you pray to statues of gods?

3Remember that the Lord has set apart his faithful servant for himself.

The Lord hears me when I call out to him.

4Tremble and do not sin.

When you are in bed,

look deep down inside yourself and be silent.

5Offer to the Lord the sacrifices that godly people offer.

Trust in him.

6Lord, many are asking, “Who will make us successful?”

Lord, may you do good things for us.

7Fill my heart with joy

when the people have lots of grain and fresh wine.

8In peace I will lie down and sleep.

Lord, you alone keep me safe.