መዝሙር 34 – NASV & NIRV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 34:1-22

መዝሙር 3434 34 የዚህ መዝሙር እያንዳንዱ ጥቅስ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀመር ሲሆን፣ ጅማሬው ወይም ጅማሬውና መጨረሻው ትርጕም የሚሰጥ ግጥም ነው።

የእግዚአብሔር ፍትሕ ውዳሴ

እንደ እብድ ሆኖ አቤሜሌክ ፊት በመቅረቡ ተባርሮ በወጣ ጊዜ የዘመረው፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔርን ሁልጊዜ እባርከዋለሁ፤

ምስጋናውም ዘወትር ከአፌ አይለይም።

2ነፍሴ በእግዚአብሔር ተመካች፤

ትሑታንም ይህን ሰምተው ሐሤት ያደርጋሉ።

3ኑና ከእኔ ጋር እግዚአብሔርን አክብሩት፤

ስሙንም በአንድነት ከፍ ከፍ እናድርግ።

4እግዚአብሔርን ፈለግሁት፤ እርሱም መለሰልኝ፤

ከፍርሀቴም ሁሉ አዳነኝ።

5ወደ እርሱ የሚመለከቱ ያበራሉ፤

ፊታቸውም ከቶ አያፍርም።

6ይህ ችግረኛ ጮኸ፤ እግዚአብሔርም ሰማው፤

ከመከራውም ሁሉ አዳነው።

7እግዚአብሔርን በሚፈሩት ዙሪያ የእግዚአብሔር መልአክ ይሰፍራል፤

ያድናቸዋልም።

8እግዚአብሔር ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እዩ፤

እርሱን መጠጊያ የሚያደርግ ምንኛ ቡሩክ ነው!

9እናንተ ቅዱሳኑ፤ እግዚአብሔርን ፍሩት፤

እርሱን የሚፈሩት አንዳች አያጡምና።

10አንበሶች ሊያጡ፣ ሊራቡም ይችላሉ፤

እግዚአብሔርን የሚሹ ግን መልካም ነገር አይጐድልባቸውም።

11ልጆቼ ሆይ፣ ኑ፤ ስሙኝ፤

እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራችኋለሁ።

12ሕይወትን የሚወድድ፣

በጎውንም ያይ ዘንድ ዕድሜን የሚመኝ ማን ነው?

13አንደበትህን ከክፉ ነገር ከልክል፤

ከንፈርህንም ከሽንገላ ጠብቅ።

14ከክፉ ሽሽ፤ መልካሙንም አድርግ፤

ሰላምን ፈልጋት፤ ተከተላትም።

15የእግዚአብሔር ዐይኖች ወደ ጻድቃን ናቸው፤

ጆሮዎቹም ለጩኸታቸው ክፍት ናቸው።

16መታሰቢያቸውን ከምድር ለማጥፋት፣

የእግዚአብሔር ፊት በክፉ አድራጊዎች ላይ ነው።

17ጻድቃን ሲጮኹ፣ እግዚአብሔር ይሰማቸዋል፤

ከመከራቸውም ሁሉ ያድናቸዋል።

18እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው፤

መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል።

19የጻድቅ መከራው ብዙ ነው፤

እግዚአብሔር ግን ከሁሉም ያድነዋል።

20ዐጥንቶቹን ሁሉ ይጠብቃል፤

ከእነርሱም አንድ አይሰበርም።

21ኀጢአተኞችን ክፋት ይገድላቸዋል፤

ጻድቃንን የሚጠሉ ይፈረድባቸዋል።

22እግዚአብሔር የባሪያዎቹን ነፍስ ይቤዣል፤

እርሱንም መጠጊያ ያደረገ አይፈረድበትም።

New International Reader’s Version

Psalm 34:1-22

Psalm 34

A psalm of David when he was with Abimelek and pretended to be out of his mind. Abimelek drove him away, and David left.

1I will thank the Lord at all times.

My lips will always praise him.

2I will find my glory in knowing the Lord.

Let those who are hurting hear me and be joyful.

3Join me in giving glory to the Lord.

Let us honor him together.

4I looked to the Lord, and he answered me.

He saved me from everything I was afraid of.

5Those who look to him have joyful faces.

They are never covered with shame.

6This poor man called out, and the Lord heard him.

He saved him out of all his troubles.

7The angel of the Lord stands guard

around those who have respect for him.

And he saves them.

8Taste and see that the Lord is good.

Blessed is the person who goes to him for safety.

9You holy people of God, have respect for the Lord.

Those who respect him have everything they need.

10The lions may grow weak and hungry.

But those who look to the Lord have every good thing they need.

11My children, come. Listen to me.

I will teach you to have respect for the Lord.

12Do you love life

and want to see many good days?

13Then keep your tongues from speaking evil.

Keep your lips from telling lies.

14Turn away from evil, and do good.

Look for peace, and go after it.

15The Lord looks with favor on those who are godly.

His ears are open to their cry.

16But the Lord doesn’t look with favor on those who do evil.

He removes all memory of them from the earth.

17Godly people cry out, and the Lord hears them.

He saves them from all their troubles.

18The Lord is close to those whose hearts have been broken.

He saves those whose spirits have been crushed.

19The person who does what is right may have many troubles.

But the Lord saves him from all of them.

20The Lord watches over all his bones.

Not one of them will be broken.

21Sinners will be killed by their own evil.

The enemies of godly people will be judged.

22The Lord will save those who serve him.

No one who goes to him for safety will be found guilty.