መዝሙር 2 – NASV & NIVUK

New Amharic Standard Version

መዝሙር 2:1-12

መዝሙር 2

መሲሓዊ ትዕይንት

1ሕዝቦች ለምን ያሤራሉ?2፥1 ዕብራይስጡ እንዲሁ ሲሆን፣ ሰብዓ ሊቃናት ግን ይቈጣሉ ይላል።

ሰዎችስ ለምን ከንቱ ነገር ያውጠነጥናሉ?

2የምድር ነገሥታት ተነሡ፤

ገዦችም በእግዚአብሔርና በመሲሑ2፥2 ወይም የተቀባው ላይ

ሊመክሩ ተሰበሰቡ፤

3“ሰንሰለታቸውን እንበጥስ፣

የእግር ብረታቸውንም አውልቀን እንጣል” አሉ።

4በሰማይ ዙፋን ላይ የተቀመጠው ይሥቃል፤

ጌታም ይሣለቅባቸዋል።

5ከዚያም በቍጣው ይናገራቸዋል፤

በመዓቱም ያስደነግጣቸዋል፤

6ደግሞም፣ “እኔ ግን በተቀደሰው ተራራዬ፣

በጽዮን ላይ የራሴን ንጉሥ ሾምሁ” ይላል።

7የእግዚአብሔርን ሕግ ዐውጃለሁ፤

እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “አንተ ልጄ ነህ፤

እኔ ዛሬ ወለድሁህ፤2፥7 ወይም …አባትህ ሆንሁ

8ለምነኝ፤

መንግሥታትን ርስት አድርጌ፣

የምድርንም ዳርቻ ግዛት እንዲሆንህ እሰጥሃለሁ።

9አንተም በብረት በትር ትቀጠቅጣቸዋለህ፤2፥9 ወይም በብረት ዘንግ ትሰባብራቸዋለህ

እንደ ሸክላ ዕቃ ታደቅቃቸዋለህ።”

10ስለዚህ እናንት ነገሥታት ልብ በሉ፤

እናንት የምድር ገዦችም፣ ተጠንቀቁ።

11እግዚአብሔርን በፍርሀት አገልግሉት፤

ለእርሱ መራድም ደስ ያሰኛችሁ።

12እንዳይቈጣና በመንገድ እንዳትጠፉ፣

ዝቅ ብላችሁ ልጁን ሳሙት፤

ቍጣው ፈጥኖ ይነድዳልና።

እርሱን መጠጊያ የሚያደርጉ ሁሉ የተባረኩ ናቸው።

New International Version – UK

Psalms 2:1-12

Psalm 2

1Why do the nations conspire2:1 Hebrew; Septuagint rage

and the peoples plot in vain?

2The kings of the earth rise up

and the rulers band together

against the Lord and against his anointed, saying,

3‘Let us break their chains

and throw off their shackles.’

4The One enthroned in heaven laughs;

the Lord scoffs at them.

5He rebukes them in his anger

and terrifies them in his wrath, saying,

6‘I have installed my king

on Zion, my holy mountain.’

7I will proclaim the Lord’s decree:

He said to me, ‘You are my son;

today I have become your father.

8Ask me,

and I will make the nations your inheritance,

the ends of the earth your possession.

9You will break them with a rod of iron2:9 Or will rule them with an iron sceptre (see Septuagint and Syriac);

you will dash them to pieces like pottery.’

10Therefore, you kings, be wise;

be warned, you rulers of the earth.

11Serve the Lord with fear

and celebrate his rule with trembling.

12Kiss his son, or he will be angry

and your way will lead to your destruction,

for his wrath can flare up in a moment.

Blessed are all who take refuge in him.