መዝሙር 140 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 140:1-13

መዝሙር 140

በክፉዎች ላይ የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ከክፉ ሰዎች አድነኝ፤

ከዐመፀኞችም ሰዎች ጠብቀኝ፤

2እነርሱ በልባቸው ክፉ ነገር ያውጠነጥናሉ፤

በየዕለቱም ጦርነት ይጭራሉ።

3ምላሳቸውን እንደ እባብ ያሾላሉ፤

ከከንፈራቸውም በታች የእፉኝት መርዝ አለ። ሴላ

4እግዚአብሔር ሆይ፤ ከክፉዎች እጅ ጠብቀኝ፤

እግሮቼንም ለመጥለፍ ከሚያደቡ ዐመፀኞች ሰውረኝ።

5ትዕቢተኞች ወጥመድ በስውር አስቀመጡብኝ፤

የመረባቸውን ገመድ ዘረጉብኝ፤

በመንገዴም ላይ አሽክላ አኖሩ። ሴላ

6እግዚአብሔር ሆይ፤ “አንተ አምላኬ ነህ” እልሃለሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ የልመና ጩኸቴን ስማ።

7ብርቱ አዳኝ የሆንህ ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤

በጦርነት ዕለት የራስ ቍር ሆንኸኝ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ የክፉዎች ምኞት አይፈጸም፤

በትዕቢትም እንዳይኵራሩ፣

ዕቅዳቸው አይሳካ። ሴላ

9ዙሪያዬን የከበቡኝ ሰዎች ራስ፣

የከንፈራቸው መዘዝ ይጠምጠምበት።

10የእሳት ፍም በላያቸው ይውረድ፤

ዳግመኛም እንዳይነሡ ወደ እሳት ይጣሉ፤

ማጥ ወዳለበት ጕድጓድ ይውደቁ።

11ምላሰኛ በምድሪቱ ጸንቶ አይኑር፤

ዐመፀኛውን ሰው ክፋት አሳድዶ ያጥፋው።

12እግዚአብሔር ለድኻ ፍትሕን እንደሚያስከብር፣

ለችግረኛውም ትክክለኛ ፍርድን እንደሚሰጥ ዐውቃለሁ።

13ጻድቃን በእውነት ስምህን ያመሰግናሉ፤

ቅኖችም በፊትህ ይኖራሉ።

Ketab El Hayat

مزمور 140:1-13

الْمَزْمُورُ الْمِئَةُ وَالأَرْبَعُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ. مَزْمُورٌ لِدَاوُدَ

1أَنْقِذْنِي يَا رَبُّ مِنَ الأَشْرَارِ وَاحْفَظْنِي مِنَ الظَّالِمِينَ، 2الَّذِينَ يَنْوُونَ عَلَى الشَّرِّ فِي قُلُوبِهِمْ وَيُثِيرُونَ الْحَرْبَ دَائِماً، 3سَنُّوا أَلْسِنَتَهُمْ كَالْحَيَّةِ، وَسُمُّ الأَصْلالِ تَحْتَ شِفَاهِهِمْ. 4احْمِنِي يَا رَبُّ مِنْ قَبْضَةِ الشِّرِّيرِ، وَأَنْقِذْنِي مِنَ الظَّالِمِينَ الْمُتَآمِرِينَ عَلَى عَرْقَلَةِ خُطْوَاتِي. 5أَخْفَى لِي الْمُتَكَبِّرُونَ فَخّاً، وَنَشَرُوا شَبَكَةً بِجَانِبِ الطَّرِيقِ، وَنَصَبُوا لِي أَشْرَاكاً.

6قُلْتُ لِلرَّبِّ: «أَنْتَ إِلَهِي» فَيَا رَبُّ أَصْغِ إِلَى صَوْتِ تَضَرُّعِي. 7أَيُّهَا الرَّبُّ السَّيِّدُ، يَا قُوَّةَ خَلاصِي، أَنْتَ وَقَيْتَ رَأْسِي فِي يَوْمِ الْقِتَالِ. 8لَا تُحَقِّقْ يَا رَبُّ رَغْبَاتِ الأَشْرَارِ، وَلَا تُنْجِحْ مَكِيدَتَهُمْ لِئَلّا يَسْتَكْبِرُوا. 9رُدَّ عَلَى رُؤُوسِ مَنْ يُحَاصِرُونَنِي مَكَائِدَ مَا يَتَكَلَّمُونَ به. 10لِيَسْقُطْ عَلَيْهِمْ جَمْرٌ مُلْتَهِبٌ، وَلْيُطْرَحُوا إِلَى النَّارِ، وَإِلَى غَمَرَاتِ اللُّجَجِ، فَلَا يَنْهَضُوا أَيْضاً. 11لَا تَدَعْ ذَا اللِّسَانِ السَّلِيطِ يَثْبُتُ فِي الأَرْضِ: فَالشَّرُّ يَتَصَيَّدُ رَجُلَ الظُّلْمِ لِيُهْلِكَهُ. 12قَدْ عَلِمْتُ أَنَّ الرَّبَّ يُنْصِفُ دَعْوَى الْمَسَاكِينِ وَيَحْكُمُ بِالْحَقِّ لِلْمُحْتَاجِينَ. 13نَعَمْ، إِنَّ الصِّدِّيقِينَ يَحْمَدُونَ اسْمَكَ، وَالصَّالِحِينَ يُقِيمُونَ فِي حَضْرَتِكَ.